Monday, August 31, 2015

ቤኒሻንጉል ክልል በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ላይ ግድያ ተፈጸመባቸው


ኢሳት ዜና (ነሐሴ 25, 2015)
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሚገኙ የአማራ ተወላጆች ላይ የተቀነባበረ ጥቃት መሰንዘሩን የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገለጹ። ባለፈው ሚያዚያ ወር መጨረሻ ተፈጸመ በተባለው በዚሁ ጥቃት፣ ከ80 በላይ ሰዎች መገደላቸውንና በአንድ ቀበሌ ውስጥ የሚገኙ አማሮች ሙሉ በሙሉ የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸውን ዕማኞች ለኢሳት ገልጸዋል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ወንበራ ወረዳ መልካ ቀበሌ ከሶስት ወራት በፊት በተፈጸመው በዚሁ ጥቃት 84 ሰዎች መገደላቸውን የገለጹት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ግድያውም በጦር መሳሪያና በስለት ጭምር የታገዘ መሆኑን አስረድተዋል። ለቀናት አማሮች የሚደርስላቸው በማጣታቸው የተረፉት ንብረታቸውን ጥለው መሸሻቸውን ገልጸዋል።
ሚያዚያ 27 እና 28 ለሁለት ቀናት በወንበራ ወረዳ መልካ ቀበሌ ለቀጠለው ጥቃት መነሻው አንድ የአካባቢው ተወላጅ ባልታወቁ ሰዎች ተገደሎ መገኘቱ እንደሆነም ተመልክቷል።
በአማሮች ላይ በአካባቢው ባለስልጣናት ግፊትና ድጋፍ ለተቀነባበረውና ለቀጠለው ጥቃት የሚደርስ አካል በመታጣቱ፣ ሰለባዎቹ ለቀናት አደጋውን ሲጋፈጡ መቆየታቸውንም መረዳት ተችሏል።
ኢሳት ያነጋገራቸው ሁለት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደገለጹት የሟቾቹ አስከሬን የተሰበሰበው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከቀናት በኋላ ወደስፍራው ሲደርሱ ነው።
ጥቃቱን በማድረስ የተጠረጠሩ 10 ያህል ሰዎች የተያዙ ቢሆንም፣ ድርጊቱን በማቀነባበርና በመምራት ተሳታፊ የሆኑ ባለስልጣናት አለመጠየቃቸውን መረዳት ተችሏል።

UNOCHA said additional fund is required to address El Niño impact in Ethiopia


ESAT News (August 31, 2015)
A report released today by the United Nation Office for the Coordination of Humanitarian Affairs (UNOCHA) showed that additional funds are required to address the impacts of El Niño in Ethiopia for the first quarter of 2016.
The statement also said that Ethiopian Ministry of Health urgently needed US$5.5 million to vaccinate 5.3 million children under-5 in nutrition hotspot priority 1 and 2 Woredas.
Low rains caused domestic animals deaths
Low rains caused domestic animals deaths
OCHA said 60% of the required funds to address the drought and famine was raised. Yet, $174 million is urgently needed where “$110 million is intended to meet the food needs of 4.5 million people; and $64 million for emergency needs in the nutrition, WASH, health, agriculture and education sectors during the remainder of 2015.”
OCHA estimates food insecurity will remain a concern in belg rain receiving areas: Southern, Central, Eastern and North-Eastern Ethiopia until the next belg harvest in June 2016.
Low belg harvest and failed or low meher rain would significantly exasperate food insecurity in these vulnerable areas, the report said. Therefore, additional funds are needed to address the extended impact in 2016.
UNOCHA predicted that displacements may occur due to flood in Afar, Oromia, Amhara, and Somali areas situated along major rivers and their tributaries. OCHA urges all authorities to closely monitor developments to mitigate the displacement.
Previously ESAT reported that belg crop producing areas did not receive adequate rains from February to May 2015 leading millions to starvation. In pastoral areas, water and pasture shortages impacted the livestock body condition, milk, and herd size.
Reports from Ethiopia indicated that crop coverage in belg-rain receiving areas was reduced to 40-60 per cent. Belg-producing areas experienced below average harvest in central Southern Nations, Nationalities, and Peoples’ Region (SNNPR) and northeastern Amhara, the lowlands of the Tekeze River catchment in northern Amhara, and the lowlands of eastern Oromia in Ethiopia.

የሱዳን ወታደሮች ኢትዮጵያውያንን በአሰቃቂ ሁኔታ ገደሉ

ነኅሴ ፳፭ (ሀያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሱዳን ባለሀብቶች መተማ ዮሃንስ ከተማ ውስጥ “ትራክተር መንዳት የሚችል 11 ሰዎችን እንፈልጋለን” የሚል ማስታወቂያ መለጠፋቸውን ተከትሎ፣ ውድድሩን ካለፉት መካካል 8ቱ በሱዳን ታጣቂዎች ታርደው ተገድለዋል።
ባለሀብቶቹ በርካታ አመልካቾችን ቢያገኙም፣ አስራ አንዱን ብቻ ይዘው ወደ ሱዳን መሄዳቸውን ፣ ይሁን እንጅ ሱዳን ውስጥ ሲገቡ፣ ወታደሮቹ መንገድ ላይ ጠብቀው ከመኪና ላይ በመውጣት ሰዎችን ማረድ ሲጀምሩ፣ የውትድርና ትምህርት የነበራቸው 3 ወጣቶች ከመኪና ላይ በመውረድ ማምለጣቸውን፣ ቀሪዎቹ በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። የተወሰኑ አስከሬዎች መቃጠላቸውን፣ የተወሰኑት ደግሞ ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ኢሳት የወረዳውን አስተዳዳሪ ለማነጋገር ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም ሊሳካለት አልቻለም።
ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ድንበር እንዲካለል ሰሞኑን በድጋሜ ጠይቃለች። ከዚህ ቀደም እጅግ ሰፊ የሆነ መሬት ከኢትዮጵያ የወሰደችው ሱዳን፣ በአንዳንድ አካባቢዎች ያሉ አወዛጋቢ ቦታዎች እንዲካለሉላት ትፈልጋለች። በኢትዮጵያውያን ላይ የተወሰደውን እርምጃ በተመለከተ የኢህአዴግ መንግስት የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እስካሁን ምንም አላለም።

1ታደለ አበጀ 
2 ቴዴ ሸመዴ 
3 የሁንሰ አሰናቀው
4 ታከለ አህመድ
5 እሸቱ ዳውድ
6 ባህሩ ቃኝው
7 ሀሰን
8 ታዮ ሙላለም










በቡሌሆራ ፖሊሶች በወሰዱት እርምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎቸ ተጎዱ


ነኅሴ ፳፭ (ሀያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነሃሴ 19 ቀን በኦሮምያ ክልል በቡሌሆራ ከተማ፣ በ1949 የተገነባውን የገበያ ማእከል በማፍረስ የመኪና መናሃሪያ ለማድረግ፣ እንቅስቃሴ በተጀመረበት ወቅት ህዝቡ ያሰማውን ተቃውሞ ተከትሎ ፖሊሶች በወሰዱት እርምጃ ከ150 በላይ ሰዎች በድብደባ ሲቆስሉ፣ ወገኖ ወንዳቸው የተባለ ወጣት በጥይት ተመትቶ ሆስፒታል ገብቶ እየታከመ ነው።
የከተማው ባለስልጣናት ከአካባቢው ነዋሪዎች ጋር ሳይስማሙና ለነጋዴዎቹ አስፈላጊውን ካሳ ሳይከፍሉ የማፍረሻ መኪኖችን በመያዝ ማፍረስ መጀመራቸውን የሚናገሩት ነዋሪዎች፣ ህዝቡ ድርጊቱን እንዳየ በባለስልጣኖቹ ላይ ድንጋይ በመወርወር ተቃውሞውን ገልጿል።
ፖሊሶች ተኩስ በመክፈት ህዝቡን ለመበተን ሙከራ ቢያደርጉም፣ ግጭቱ ለሰአታት ቆይቷል። በፖሊስ ዱላና ጥይት የቆሰሉት በአንቡላንስ እየተጫኑ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።
ይህንን ተከትሎ ፖሊሶች እስከ ሌሊት ድረስ ወደ መኖሪያ ቤቶች እየገቡ ነፍሰጡሮችን ሳይቀር ደብድበዋል። በእለቱ 26 ሰዎች ሲታሰሩ፣ 13 ተለቀው፣ 13 ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
አቶ ታደለ ቢቂላ የተባሉ አባት ልጃቸው ታደለ ቢቂላ ክፉኛ መደብደቡን ተከትሎ ወደ ሆስፒታል ሲሄዱ፣ ልጄን ፖሊስ ደብድቦብኝ ነው ብለው በመናገራቸው የተባሱጩት ፖሊሶች እርሳቸውንም ከ13ቱ ተከሳሾች መካከል በመቀላቀል ፍርድ ቤት አቅርበዋቸዋል።
የዞኑ የሰማያዊ ፓርቲ ተወካይ የሆኑት አቶ ጌታቸው በቀለ፣ ፖሊስ የወሰደውን እርምጃ አውግዘዋል። ለተጎዱት ቤተሰቦች አስቸኳይ ካሳ እንዲከፈላቸው አቶ ጌታቸው ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ ከምርጫው በሁዋላ ከ2 ሺ ያላነሱ የኦሮሞ ተወላጆች መታሰራቸውን የምስራቅ አፍሪካ የሰብአዊ መብት ሊግ ገልጿል።
ሊጉ ባወጣው መግለጫ በቡሌ ሆራ፣ ደምቢ ዶሎ፣ ምእራብና ሰሜን ሸዋ ዞን አፈሳው ተጧጡፏል።
በዋራ ጃርሶ ወረዳ ከ400 በላይ አርሶአደሮች አመጽያንን አስጠግታችሁዋል በሚል መታሰራቸውን አስታውቓል። ከታሰሩት መካካል የ20 ሰዎችን ስም ይፋ አድርጓል።

በርካታ የትግራይ ህዝብ ለርሃብ ተጋርጦ ባለበት ሰአት ህወሃት 2 ሺ እንግዶችን በውስኪና በቁርጥ ስጋ አንበሸበሸ


ነኅሴ ፳፭ (ሀያ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የክልሉ ወኪላችን እንዳለው ባለፈው ቅዳሜ ህወሃት ለኢህአዴግ ጉባኤተኞች ባዘጋጀው የእራት ግብዣ፣ ከ2 ሺ ያላነሰ ሰው ተገኝቷል። ለእንግዶቹ የተለያዩ ምግቦች፣ ቁርጥ ስጋ እና ውስኪ እንደ ልብ ቀርቦላቸዋል።
ግብዣው የተደረገው 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ህዝብ የሚላስና የሚቀመስ እንደሌለው ሪፖርት በተደረገበት ወቅት ነው። በትግራይ የተለያዩ ቦታዎች ከፍተኛ ድርቅ መግባቱን ሪፖርቶች ያስረዳሉ።
ኢህአዴግ ለተለያዩ በአላት ግብዣዎች በእየአመቱ በቢሊዮን የሚጠጋ ብር ያወጣል። በሌላ በኩል ኢህአዴግ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝን በድጋሜ ሊቀመንበር፣ አቶ ደመቀ መኮንንን ደግሞ ም/ል ሊቀመንበር አድርጎ መርጧል።
በሌላ በኩል አቶ ሃይለማርያም በሰቆጣ የአሸንዳን በአል ለማክበር የሚገኙ ሲሆን፣ በአሉ ካለፈ ቀናት ቢቆጠሩም፣ ሴቶች ለበአሉ ሲባል ሹሩባቸውን እንዳይፈቱ ታዘዋል።
በአሉ የሚከበረው በከተማው ውስጥ በድርቁ ምክንያት ውሃ በጠፋበት እና በርካታ ህዝብ ” በጭንቀት ተውጦ በሚገኝበት ወቅት ነው። የአቶ ሃይለምርያም ጉብኝት በአካባቢው ድርቅ አለመግባቱን ለማሳየት ተብሎ የተዘጋጀ ነው። ይሁን እንጅ ኢሳት በአካባቢው ከፍተኛ የሆነ ችጋር መከሰቱን ከነዋሪዎች አንደበት ለማረጋገጥ ችሏል። ይህንን በተመለከተ ያጣነቀረውን ዘገባ ነገ ያቀርበዋል።

Ethiopia recorded highest inflation rate in Africa after Malawi, Sudan in July 2015


August 31, 2015
BY RICHARD MUNGAI

MALAWI, Sudan and Ethiopia recorded an inflation rate of 26.6, 17.4 and 14.7 per cent each in July, making them the countries with the most expensive goods and services in the Comesa region, according to the latest harmonised consumer price indices.

The data provided by the Common Market for East and Southern Africa shows a high inflation rate also prevailed in Burundi, Madagascar and Egypt at 8.5, 7.8 and 7.7 per cent, respectively.

The Democratic Republic of Congo recorded a low inflation rate of 0.6 per cent while Mauritius, Rwanda and Zimbabwe recorded negative 0.2, 2.3 and 2.8 each.

Zambia, Kenya, Seychelles, Uganda and Swaziland, which recorded an inflation of 6.2, 6, 5.7, 5.5 and 4.6 per cent respectively, were the only countries that maintained the recommended inflation average of two to seven per cent.

According to the index, inflation in the Comesa region stood at 7.3 per cent in July 2015.

It shows an item that cost an average of 100 cents in July 2014 would have sold at 107.30 cents in July this year if the region used a common currency.

“The year-on-year inflation rate in the Comesa region as measured by the HCPI-Comesa stood at 7.3 per cent for the month of July 2015, down from 9.5 per cent registered in June 2015,” it states.

“The month on month inflation rate in the Comesa region as measured by HCPI-Comesa stood at 0.7 per cent for the month of July 2015, up from 0.2 per cent registered in June 2015. It was 2.8 per cent in July 2014.”

The HCPI-Comesa annual rate measures the price change between a particular month and the same month one year earlier while the monthly rate measures the price change between the two latest months.

The index shows the main components of expenditure in the region are education, recreation and culture and alcoholic and tobacco.

Others include restaurants and hotels, food and non-alcoholic beverages, clothing and footwear, housing, water, electricity, gas and other fuels, furnishings, household equipment and routine maintenance, health, transport and communication.

– See more at: http://www.the-star.co.ke/news/july-cost-living-highest-malawi-sudan-and-ethiopia?#sthash.dJ6i5vkK.dpuf

Friday, August 28, 2015

Sudanese official calls for ending border disputes with Ethiopia


governor of Gedaref state, Merghani Salih, has called for redrawing borders between Sudan and Ethiopia in order to bring the long running dispute between the two nations to an end.

A road leading to Ethiopia-Sudan border (Photo Jamminglobal.com)
Farmers from two sides of the border used to dispute the ownership of land in the Al-Fashaga area located in the south-eastern part of Sudan’s eastern state of Gedaref.

The two governments have agreed in the past to redraw the borders, and to promote joint projects between people from both sides for the benefit of local population. However, the Ethiopian opposition has used to accuse the ruling party of abandoning Ethiopian territory to Sudan.

In November 2014, Sudan’s president Omer al-Bashir and Ethiopia’s premier, Hailemariam Desalegn, instructed their foreign ministers to set a date for resuming borders demarcation after it had stopped following the death of Ethiopia’s former prime minister, Meles Zenawi.

Also, in December 2013 the Joint Sudanese- Ethiopian Higher Committee (JSEHC) announced that it reached an agreement to end disputes between farmers from two sides of the border over the ownership of agricultural land particularly in the Al-Fashaga.

Salih on Friday emphasized to a federal delegation from the societal and popular police currently visiting Gedaref the need to redraw the Sudanese-Ethiopian borders in order to end land disputes permanently.

He pointed to the importance of the joint military patrols to secure the borders between the two countries, praising the role of the societal and popular police in protecting the borders.

It should be mentioned that Al-Fashaga covers an area of about 250 square kilometers and it has about 600.000 acres of fertile lands. Also there are river systems flowing across the area including Atbara, Setait and Baslam rivers.

Sudan’s Gadarif and Blue Nile states border Ethiopia’s Amhara region. The borders between Sudan and Ethiopia were drawn by the British and Italian colonisers in 1908.

Source:: Debirhan

በቃሉ ወረዳ አንድ ሰው በታጣቂዎች ተገደለ


ነኅሴ ፳፪ (ሀያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ወሎ ዞን በቃሉ ወራዳ ጅጋ ቀበሌ ላይ ጀማል ሙሼ የተባለ የ22 ዓመት ወጣት፣ ሃምሌ 27 ቀን 2007 ዓም በሚሊሺያዎች ተገድሏል። ወጣት ጀማል ሙሼ በዩ፣ ሰይድ ሙሄ ጌሮና እንድሪስ ኡመር በተባሉ ታጣቂዎች ተገድሎ ከአካባቢው 24 ኪሎሜትር ርቆ ሊቀበር ሲል መረጃ የደረሳቸው ዘመዶቹ ቦታው ድረስ በመሄድ አስከሬኑን ወስደዋል።
ወጣቱ ግንባሩ አካባቢ በጥይት የተመታ ሲሆን፣ ሁለቱ ኩላሊቶቹም ወጥተዋል። ታጣቂዎቹ ወጣቱን ብረታብረት እንሸጥልሃለንና 40 ሺ ብር ይዘህ ና ብለው እንዳስመጡት፣ ነገር ግን ቦታው ደርሶ በዋጋ ለመስማማት አለመቻሉን ዘመዶቹ ለኢሳት ተናግረዋል። ሌሎች ጉደኞቹ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ፣ ታጣቂዎቹ ጀማልን መንገድ ላይ በማስቆም በጥይት ገድለው ገንዘቡንና የእጅ ስልኩን ይዘው በመሄድ ለመቅበር ሲሞክሩ ዘመዶቹ ደርሰዋል።
ታጣቂዎቹ እንዲያዙ ዘመዶቹ ለመንግስት አቤት ቢሉም የሚሰማቸው ማጣታቸውንና ገዳዮቹ አሁንም ድረስ ስራቸውን እየሰሩ መሆኑን አለም ይወቅልን ሲሉ ቤተሰቦቹ ተናግረዋል። በጉዳዩ ዙሪያ የወረዳውን ባለስልጣናት ለማናገር ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።

Source:: Ethsat

ለምርጫ ተብለው የተቀየሩ ትራንስፎርመሮች ተቃጥለው በርካታ ሰዎች ተጎዶ


ነኅሴ ፳፪ (ሀያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ኦሞ ዞን ከምርጫ 2007 ጋር በተያያዘ የተቀየሩ በርካታ ትራንስፎርመሮች በአንድ ቀንና ሰአት በመቃጠላቸው ሰዎች ተጎድተዋል።
በነ ጸማይ ወረዳ ቃቆ ቀበሌ ትራንስፎርመሩ ሲቃጠል አንድ ነርስ ወዲያውኑ ህይወቱን ሲያጣ፣ 11 ሰዎች ደግሞ ክፉኛ ቆስለዋል።
በዚሁ ወረዳ ቀይ አፈር ከተማ ላይ ተጨማሪ 3 ትራንስፎርመሮች ሲፈነዱ፣ በሀመር ወረዳ በዲመካ ከተማ አንድ ትራንስፎርም፣ በጂንካ ከተማም እንዲሁ ሌላ ትራንስፎርመር ተቃጥሎአል።ሁሉም ትራንስፎርመሮች በተመሳሳይ ሰአት ነው የተቃጠሉት። ነዋሪዎች ፍንዳታው ከጥራት ችግር ጋር በተያያዘ የተከሰተ መሆኑን ገልጸው፣ እስካሁን ለተጎጂዎች እርዳታ አለመድረሱንም ተናግረዋል።
የተቃጠሉት ትራንስፎርመሮች በቅርቡ ከቻይና የገቡት ይሁኑ ወይም የመከላከያ ኢንጂነሪንግ የገጣጠማቸውና ለመብራት ሃይል ያስረከባቸው በውል አልታወቀም። ይሁን እንጅ ሁሉም ትራንስፎርመሮች ምርጫ ሊካሄድ አንድ ወር ሲቀረው መቀየራቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል። በጉዳዩ ዙሪያ የዞኑን ባለስልጣናት ለማናገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

Source:: Ethsat

ኢህአደግ ጥራት ያለው አባል ማግኘት አልቻልኩም አለ


ነኅሴ ፳፪ (ሀያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ 10ኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን በመቀሌ ከተማ ሰማእታት አዳራሽ ዛሬ ሲጀምር በጽሁፍ ባሰራጨው ሪፖርቱ የአባላት ጥራት ችግር እንደገጠመው ይፋ አደርጓል።
ሪፖርቱ እንደሚለው አባላት ስለድርጅቱ ታሪክ ፣ፕሮግራም፣እሴቶችና ህገደንብ ዝርዝር ግንዛቤ ሳይዙ የሚመለመሉበት ሁኔታ አለ። “በእኛና በተቃዋሚዎች መካከል ስላለው መሰረታዊ ልዩነት ፣ስለመድረኩ ባህሪና ፈተናዎቹ በቂ መነሻ እውቀት ይዘው የእጩነት ጊዜያቸውን አጠናቀው ወደሙሉ አባልነት እንዲሸጋገሩ ለማድረግ የሚሰራው ስራም ከጉድለት የተላቀቀ አይደለም። ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ አባላትም ለጥቅም ማግኛ አማትረው ድርጅቱን የሚቀላቀሉ ናቸው” ሲል አማሮአል።
በእነዚህና ተያያዥ ጉዳዮች ምክንያት ጥራት ያለው አባል መጥፋቱን የሚያወሳው ይህ ሪፖርት፣ በአሰላለፍ ረገድ የጎራ መደበላለቅ ማጋጠሙንም ጠቅሷል። በመንግስት ፖሊሲዎችና ልዩ ልዩ ሰነዶች ስልጠናዎች በተሰጠበት ወቅት፣ በመንግስት መ/ቤቶችና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ባሉ አባላት የሚነሱ የተሳሳቱ አመለካከቶች አባል ካለሆነው ብዙም የተለዩ የማይሆኑበት ሁኔታ በስፋት መታየቱን ለአብነት አንስቷል።
የግንባሩ አባላት ጠባብነትና ትምክህተኝነትን እንዲሁም በሃይማኖት ሽፋን የሚከሰት አክራሪነትን በበቂ ሁኔታ ለመመከት የሚቸገር ፣አልፎ ተርፎም የእነዚህ አመለካከቶች ሰለባ ሆነዋል ሲል ይተነትናል።
ሲቪል ሰርቪስ ውስጥ የተጀመሩ ስራዎች መደናቀፋቸውን የሚያትተው ኢህአዴግ፣ “የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ስራዎች ያመጡት ለውጥ ቢኖርም ከጥራት ጉድለት ጋር ተያይዞ የሲቪል ሰርቪስ ተቁዋማት መሆን በሚገባቸው ደረጃ ላይ አለመድረሳቸው አባላችን ግንባር ቀደም ሆኖ ከሌላው ሰራተኛ በተለየ አኩሃን የተጫወተው ሚና ፣አለመኖሩን ያሳያል” በማለት የድርጅት አባላቱ ያላቸውን የጽናትና የብቃት ችግር አስቀምጦአል።
በጀማሪ ደረጃ የሚገኙ አመራሮች ግንዛቤያቸው ዝቅተኛ ሆኖ መገኘቱንም ሪፖርቱ አመልክቶአል። ለመካከለኛና ጀማሪ አመራሩ ከተሰጡ ስልጠናዎች በተገኘ መረጃ መሰረት ጀማሪ አመራሩ በግንባሩ ፖሊሲዎች ላይ ያለው ግንዛቤ አነስተኛ ከመሆኑም በተጨማሪ የሚያነሱዋቸው አንዳንድ ጉዳዮች ከኪራይ ሰብሳቢ ተቃዋሚ ሃይሎች አጀንዳዎች የማይለዩ ናቸው ሲል የገዛ አባላቱን ኮንኖአል።
ብአዴንን በ2007 ዓም ከተቀላቀሉ ከ200 ሺ አባላት መካካል ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ድርጅቱን ለቀው መሄዳቸውን ብአዴን በሪፖርቱ አመልክቷል።
ሪፖርቱ ኢህአዴግ በየቀኑ የሚሰራው የፕሮፓጋንዳ ስራ በአባላቱ ጭምር ተቀባይነት እንዳላገኘ በተቃራኒው የተቃዋሚዎች አጀንዳ በኢህአዴግ አባላት ጭምር እየተደገፈ መምጣቱን የሚያመለክት ሆኗል። የገዛ አባሎቹ የድርጅቱን መርሆዎች ካልተቀበሉና ካላመኑባቸው፣ የሌላው ህዝብ ስሜት ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት አይከብድም በማለት ዘጋቢያችን አስተያየቱን አስፍሯል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በርካታ የህወሃት ደጋፊ ወጣት አባላት ህወሃትን እየነቀፉ ነው። ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የትግራይ ወጣቶች አንዳንድ የህወሃት መሪዎችን እያነሱ በማህበራዊ የመገናኛ ዘዴዎች እየተቹ ነው። ቀድሞ ህወሃት አይነካብን ይሉ የነበሩ ደጋፊዎች፣ በሰሞኑ ጉባኤ አቶ አርከበ እቁባይ የድርጅቱ ሊቀመንበር ሆነው እንዲመረጡ ቅስቀሳ ሲያደርጉ ሰንብተዋል። ይሁን እንጅ አቶ አባይ ወልዱ ሊቀመንበር ሆነው መውጣታቸው እንደታወቀ፣ ወጣት ደጋፊዎች ” በትግራይ ተጨማሪ 5 የባርነት አመታት” በማለት ተቃውሞአቸውን እያሰሙ ነው። ህወሃት ከ15 ዓመታት ወዲህ እንዲህ አይነት ጠንካራ ክፍፍልና ነቀፌታ በአባለቱ ዘንድ ሲያጋጥመው ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

Source:: Ethsat

እስካሁን 1.2 ቢሊዮን የጨረሰው ተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ ለማለቅ ተጨማሪ ብድር ያስፈልገዋል ተባለ


ኢሳት ዜና (ነሐሴ 21 ፣ 2007)

ግንባታው ለ 12 አመታት ያህል ሲካሄድ የቆየውና የእዳ መጠኑ 1.2 ቢሊዮን ብር አካባቢ የደረሰው የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ ተጨማሪ ብድር ካልጸደቀለት በስተቀር ስራውን በተያዘለት እቅድ መሰረት እንደማይጀምር ምንጮት ለኢሳት ገለጡ።

መንግስት የተንዳሆ የስኳር ልማት ፕሮዳክሽን በአምስት አመት የልማት እቅድ መሰረት ወደማምረት ደረጃ ለማሳደግ ቢጥርም ግንባታው በተለያዩ አስተዳደራዊ ችግሮች ሊያልቅ አለመቻሉን የልማት ባንክ ምንጮች ገልጸዋል።

የህንዱ ኩባንያ ስራውን እንዲጀምር በህንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት ገነት ዘውዴ ሁኔታዎችን ማመቻቸታቸውን የተናገሩት ምንጮች፣ ኩባንያው በቂ አቅም ሳይኖረው በጉቦ ስራውን እንዲረከብ መደረጉን አስረድተዋል።

የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ አቶ ሶፊያን አህመድ የ 30 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ማፅደቃቸው የሚታወቅ ሲሆን በወቅቱ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር የነበሩት አምባሳደር ግርማ ብሩ ከፕሮጀክቱ ጋር ንክኪ እንዳልነበራቸው የልማት ባንክ ምንጮች ገልጸዋል።

የከተማና ልማት ኮንስትራክሽን ምክትል ሚኒስትር የነበሩት አቶ አርከበ እቁባይ ለስኳር ፋብሪካው ግንባታ ለሰራተኞች መኖሪያ ቤትና ለሌሎች ስራዎች የሲሚንቶና የብረታ ብረት አቅርቦቱን ስራ እንዲመሩ ሃላፊነት ተሰጥቷቸው እንደነበረም ታውቋል።

ይሁንና ሚኒስትሩ ከንግድ ሸሪኮቻቸው እንዲሁም ከመንድማቸው አቶ ጌታቸው እቁባይ ጋር በመሆን የተገዙ በርካታ ቶን ሲሚንቶዎችና ብረታ ብረቶችን ከፍተኛ የኢምፖርት ዋጋ ማቅረባቸውን ምንጮች አስረድተዋል።

ከዚሁ ድርጊት ጋር በተገናኘም አቶ ጌታቸው እቁባይና ሌሎች ግብረ-አበሮቻቸው ለእስር ተዳርገው እንደነበር ያወሱት እነዚሁ ምንጮች ሚኒስትሩ አቶ አርከበ ከከተማ ልማትና ቤቶች ሃላፊነታቸው እንዲዛወሩ ውሳኔ መተላለፉን አስታውቀዋል።

ከሙስና ጋር በተያያዘ የስኳር ፕሮጄክቱ የዘገየ ቢሆንም አሁን ተጨማሪ ብድር ካልፀደቀ ፕሮጄክቱ በተያዘለት እቅድ ስራውን ሊጀምር ኣንደሚችል ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት ለኢሳት ገልጸዋል።

Source:: Ethsat

Thursday, August 27, 2015

አንድ የመከላከያ አባል የነበረ በፖሊሶች ተደብድቦ አይኑ ጠፋ


ነኅሴ ፳፩ (ሀያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሃምሌ 27 ቀን 2007 ዓም በደቡብ ክልል በጋሞጎፋ ዞን በጫኖ ሚሌ ቀበሌ ውብዬት ጩበሮ የተባለ የመከላከያ ሰራዊት አባል ፣ መከላከያን በመልቀቅ ወደ ቤተሰቦቹ ከተመለሰ ከሁለት ወር በሁዋላ፣ ፖሊሶች አንተ ተቃዋሚዎችን ትደግፋለህ ብለው በሰደፍ ደብድበው አንድ አይኑን እንዳፈሰሱት አባቱ አቶ ጩበሮ ጩኮ ለኢሳት ተናግረዋል።
ወታደሩ ወደ ቀየው ከተመለሰ በሁዋላ፣ ከአባቱ ጋር እርሻ ስራ እየሰራ ትምህርቱንም ለመቀጠል ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅት 5 ፖሊሶችና ታጣቂዎች በጋራ በመሄድ ክፍኛ ደብድበው እራሱን እስኪስት ድረስ ደብድበውታል። ወታደሩ ወደ ሆስፒታል በተወሰደበት ወቅት፣ ዶ/ር አንዱ አይን መጥፋቱን ማረጋጋጡንና ሁለተኛውን አይኑን ለማዳን ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸውንና አሁንም ድረስ ህክምና እያደረጉለት መሆኑን አቶ ጩበሮ አስረድተዋል።
ፖሊስ ደርቅቴ ደራራ፣ ያልቄ የቴሌ፣ አለማየሁ አላሮ፣ ዘካሪያስ ፈንታና ሚሊሺያ ጳውሎስ የተባሉ ግለሰቦች ልጃቸውን መደብደባቸውን የሚናገሩት አባት፣ ጉዳዩን ለከፍተኛ ባለስልጣናት ለማመልከት እንዲሁም ወደ ፍርድ ቤት ለመውሰድ ሙከራ ቢያደርጉም፣ መልስ የሚሰጣቸው አካል በመጥፋቱና በየቀኑ በሚደርስባቸው ዛቻ ምክንያት ለህይወታቸው በመስጋት አርባምንጭ ከተማ ዘመዶቻቸው ቤት ለማደር ተገደዋል።
ፖሊሶቹ ወደ ሆስፒታል እየሄዱ በሚፈጥሩት ጫና ከሃኪሞች ጋር መጋጨታቸውንም አቶ ጬበሮ ገልጸዋል። በጉዳዩ ዙሪያ የወረዳው ባለስልጣናትን ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

Source :Esat

በአዲስ አበባ ወረዳ 9 17 የንግድ ድርጅቶች ታሸጉ


ነኅሴ ፳፩ (ሀያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነጋዴዎች ለኢሳት እንደገለጹት፣ የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት በድንገት በመምጣት በጉለሌ ክፍለከተማ ወረዳ ዘጠኝ ቀበሌ 02 የሚገኘውን የንግድ ድርጅታቸውን አሽገውባቸዋል። “በቂ ምክንያት ሳይኖርና በቂ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሳይሰጠን፣ ከአንድ ወር ላላነሰ ጊዜ ስራ ፈተን ቤተሰቦቻችን ለችግር ተጋልጠዋል” በማለት የሚናገሩት ነጋዴዎች፣ ጉዳዩን ለተለያዩ ባለስልጣናት ቢያመለክቱም መፍትሄ የሚሰጣቸው አላገኙም።
የወረዳው የኢህአዴግ ጽ/ቤት ወኪል የሆኑት አቶ ተክለአብ፣ ነጋዴዎቹ ራሳቸው እንዲሰሩበት የተሰጣቸውን ቦታ ለሶስተኛ ወገን አከራይተዋል በሚል ድርጅታቸው መታሸጉን አምነው፣ ተሰጠ የተባለው የማስጠንቀቂያ ጊዜ አጭር መሆኑን እንደሚያምኑ፣ ነገር ግን እስካሁን ሲሰራበት የነበረ አሰራር በመሆኑ ምንም ማድረግ እንደማይቻል ገልጸዋል።
ነጋዴዎቹና ቤተሰቦቻቸው ውሳኔ አጥተው ለአንድ ወር በላይ መጉላላታቸው ተገቢ ነው ወይ ተብለው ለተጠየቁት፣ ሃላፊው ተገቢ አለመሆኑንና ሌሎች አመራሮች አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጡዋቸው ግፊት እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

Source :Esat

የተቃዋሚ አባላትን እያደኑ ማሰሩ እንደቀጠለ ነው


ነኅሴ ፳፩ (ሀያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዛሬ ነሃሴ 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በምዕራብ ጎጃም ዞን ሜጫ ወረዳ አብዮት ፋና ቀበሌ ሶስት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ታድነው መታሰራቸውን የዞኑ የፓርቲው አስተባባሪዎች ገልጸዋል፡፡
ሶስቱም የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ከሌሊቱ 11 ሰዓት ጀምሮ ቤታቸው በታጣቂ ተከቦ እንዳደረ የተገለፀ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በቀበሌው ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደሚገኙ ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። ታድነው የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ተመስገን የኔሀብቴ፣ ማስተዋል አዱኛና ሙሉ አለየነው ሲሆኑ ሌሎች አባላትም እየታደኑ ነው ተብሏል፡፡
በዞኑ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የቀበሌ መታወቂያ ሲጠይቁ ‹‹የእኛ አባል ካልሆንክ አንሰጥህም›› እንደሚባሉ የጠቀሱት አስተባባሪዎቹ፣ አቶ ተመስገን የኔሀብቴ መታወቂያ በጠየቀበት ወቅት የቀበሌው ሊቀመንበር ‹‹የእኛ አባል ካልሆንክ መታወቂያ አልሰጥህም›› በማለታቸው፣ እሱም ‹‹መብቴ ነው!›› ብሎ በመከራከሩ ነሃሴ 11 ቀን 2007 ዓ.ም፣ እያስፈራራኝ ነው፣ ብለው እንዳሳሰሩትና ነሃሴ 18 ቀን 2007 ዓ.ም. 1,500 ብር ዋስ አስይዞ ከእስር ተለቅቆ እንደነበር ተገልጾአል፡፡
በተመሳሳይ በአርሲ በቆጅ የሰማያዊ ፓርቲን ወክለው ለክልል ምክር ቤት የተወዳደሩትና የሰርቦ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጃዋሩ ገልገሉ በፖለቲካ አመለካከታቸው ምክንያት የመንግስት አግልግሎት እንደማያገኙና በፖሊስ ተይዘው መታወቂያቸውን ተነጥቀዋል። ‹‹የሰማያዊ ፓርቲ አባል ስለሆንኩ መታወቂያየን በግድ ነጥቀውኛል፡፡ ይህ የእኛ መታወቂያ ነው ምንም አታመጣም ሂድና ሰማያዊ ፓርቲ ይስጥህ!›› እንደተባሉ ጋዜጣው ዘግቧል።

Source :Esat

በሃማስ የታገተው ኢትዮ እስራኤላዊ ቤተሰቦች የጋዛን መተላለፊያ ዘጉ


ነኅሴ ፳፩ (ሀያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው ዓመት መስከረም ወር ላይ በጋዛ ሰርጥ በሃማስ የታገተው ኢቲዮ እስራኤላዊ ወጣት አቭራም መንግስቱ ከሃያ በላይ የሚሆኑ ቤተሰቦቹ ልጃችን ይለቀቅ በማለት በጋዛ ኤርዝ መተላለፊያን ዘግተው ተቃውሟቸውን እያሰሙ ሲሆን የልጃቸውን መታገት በዓለማቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እንዲታወቅላቸውም ተማጽዕኖዋቸውን አሰምተዋል።
የአቭራም ወንድም ”እኛ በነፃነት የመዘዋወር መብትን እናከብራለን፣ ሁላችንም ፍልስጤማዊያንም እስራኤላዊያንም ጭምር እኔ አሁን የምንጠይቀው ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ወንድሜን ሃማስ እንዲለቅልኝ ብቻ ነው።” ብሎአል።
ሃማስ በበኩሉ የታጋቹ ቤተሰቦች ልጃቸው የዐዕምሮ ሕመም ችግር እንዳለበት ያቀረቡትን ተማጽኖ ግድ እንደማይሰጠው አስታውቋል።
ቤተ እስራኤላዊያን እስራኤል ውስጥ መድሎና መገለል እንደሚደርስባቸውና የእስራኤል መንግስት ጉዳዩን ትኩረት ሰጥቶ ያልተከታተለው በቆዳ ቀለሙ የዘረኝነት ሰለባ በመሆኑ ነው በማለት መናገራቸውን ዘ ጀሩሳሌም ፕሬስ አክሎ ዘግቧል።

Source : Esat

ህወሃቶች የአቶ መለስን የመተካካት ፖሊሲ ሲቀለብሱ ብአዴኖች ደግሞ አቶ በረከትን በማእከላዊ ኮሚቴ አባልነት ይዘው ለመጓዝ መሰኑ


ነኅሴ ፳ (ሀያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሟቹ ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ያስቀመጡት የመተካካት ፖሊሲ በህወሃት ነባር አመራሮች ሲተች፣ ብአዴኖች ፖሊሲውን ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ማድረግ ባለመቻላቸው ግራ ተጋብተዋል። የአቶ መለስ የመተካካት ፖሊሲ በ2007 ዓም ሁሉም የድርጅቱ ነባር አመራሮች በአዳዲስ ወጣት አመራሮች ይተካሉ የሚል ነበር። ይሁን እንጅ ህወሃት እያካሄደ ባለው መደበኛ ጉባኤ በአቶ መለስ ወቅት ከአመራር ቦታቸው የተነሱት ነባር ታጋዮች በጉባኤው እንደገና በመምረጥና በመመረጥ መብት እንዲሳተፉ ተደርጓል። ከህወሃት ስልጣን ተገለው የነበሩት አቶ ስብሃት ነጋ፣ ስዩም መስፍን፣ አርከበ እቁባይ፣ ብርሃነ ገብረከርስቶስና ሌሎች 17 የቀድሞ ታጋዮች በጉባኤው በታዛቢነት እንዲገኙ ቢጋበዙም፣ የጉባኤው አባላት ግለሰቦቹ በመተካካት ስም ተገፍተው ወጥተዋል ስለዚህም በሙሉ ስልጣን ይሳተፉ የሚል ጥያቄ በማቅረባቸው፣ ጉባኤው የመተካካቱን ፖሊሲ በመቀልበስ እንዲሳተፉ ወስኖላቸዋል።
የደህንነት ሹሙ ጌታቸው አሰፋ፣ የመተካካት ፖሊሲው ተቀናቃኞችን ለመግፋት ተብሎ የወጣ ነው ብለው መናገራቸውን የህወሃት አባላት እየገለጹ ሲሆን፣ ፖሊሲው እንከን የለበትም፣ በመተካካት ስም አንድም ሰው አልተገፋም፣ ተገፋሁ ያለ ሰው ካለ ይናገር በማለት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ብቻ የቀድሞ ባለቤታቸውን ፖሊሲ ከትችት ለመከላከል ደፍረው አስተያየት ሰጥተዋል። ይሁን እንጅ አቶ ስዩም መስፍን ” እሳቸው ራሳቸው ሳያምኑበት ተገፍተው እንደወጡ” ንግግር ማድረጋቸውን የህወሃት ደጋፊዎች በማህበራዊ ድረገጾች ጽፈዋል።
አቶ ስዩም መስፍን ከሶስት አመት በፊት ለኢቲቪ እና ኤስቢስ ለተባለ የውጭ ሬዲዮ በሰጡት ቃለምልልስ ፣ እርሳቸውም ሆኑ ሌሎች አመራሮች የመተካካት ፖሊሰውን አምነውበት ስልጣናቸውን መልቀቃቸውን ተናግረው ነበር። ይሁን እንጅ ቃላቸውን አጥፈው፣ አሁን “ተገፍቼ ሳላምንበት ወጣሁ” ማለታቸው የሰውየውን ማንነት፣ የአገሪቱን መሪዎች ስብእናና አቶ መለስን ምን ያክል ይፈሩዋቸው እንደነበር አመላካች ነው የሚሉ አስተያየቶች እየቀረቡ ነው።
በተመሳሳይ መንገድ መተካካቱ ለ2 አመታት ሲመከርበት ቆይቶ ሁሉም የድርጅቱ መሪዎች ተስማምተውበት ተግባራዊ ማድረጋቸውን የገለጹት አቶ አርከበ እቁባይ፣ ከአምስት አመታት በሁዋላ የተናገሩትን አጥፈው እንደገና ተመልሰዋል።
ወትሮውንም በመተካካት ፖሊሲ ስም የሚደረገውን የማባረር ዘመቻ ሲቃወሙ የቆዩት አቶ ስብሃት ገብረእግዚአብሄር በጉባኤ ባለሙሉ መብት ሆነው መሳተፋቸው፣ ከመለስ ሞት በሁዋላ ሲያደርጉት ሲሰሩት የነበረው የፖለቲካ ስራ መሳካቱን የሚያሳይ ነው። ነባር አመራሮቹ ወደፊት መምጣታቸው የሃይል አሰላለፉን ይቀይረው አይቀይረው አልታወቀም ይሁን እንጅ ወ/ሮ አዜብ መስፍን ብቻ የመለስ ራእይ ተከራካሪ ሆነው መቅረባቸው ፣ የመለስን ራእይ እናስቀጥላለን በሚል ሲገባ የነበረው ቃል ወደ ጎን መባሉን እንዲሁም የመለስ ሌጋሴ እየተቀበረ መምጣቱን እንደሚያሳይ አስተያየቶች እየተሰነዘሩ ነው።
በህይወት ካሉት የብአዴን መስራቾች መካከል እስካሁን ድረስ ከድርጅቱ ጋር የተጓዙት አመራሮች፣ በጤናና በተለያዩ ሰበቦች ስልጣናቸውን የለቀቁ ሲሆን፣ ከድርጀቱ መስራቾች መካከል አቶ በረከት ስምኦን ብቻ በማእከላዊ ኮሚቴ አባልነት እንዲቀጥሉ ተወስኗል። አቶ በረከት ቀድም ብሎ በኢሳት እንደተዘገበው ከብአዴን የስራ አስፈጻሚነትና ከኢህአዴግ የምክር ቤት ስልጣናቸው ተነስተዋል። ይሁን እንጅ እንደ አቶ አዲሱ ለገሰ ወደ ተራ አባልነት ከመውረድ በማእከላዊ ኮሚቴ አባልነት መቆየትን መርጠዋል።
ኦህዴድ ቀድም ብሎ ያሰናበታቸውን እነ አባዱላ ገመዳን መልሶ ወደ ስልጣን አላመጣም። በስራ አስፈጻሚት የተመረጡት አብዛኞቹ ቀድም ብሎ በስልጣን ላይ የነበሩት ናቸው።
ብአዴንና ኦህዴድ ነባር አመራሮቻቸውን እየቀነሱ፣ ህወሃት ነባር አመራሮችን ወደ ስልጣን የሚያመጣበት አሰራር በኢህአዴግ ውስጥ ብዥታና አለመተማመን ሊፈጥር ይችላል ሲል ዘጋቢያችን አስተያየቱን አሰፍሯል።
ሪፖርተር ጋዜጣ ባወጣው ዘገባ ደግሞ በህወሃት ጉባኤ ላይ አንድ የሃይማኖት አባት ፣ የድርጅቱ መሪዎች ቀድሞ አንግተውት የነበረውን ዓላማ እንደረሱ፣ ፍትሕ በገንዘብ እየተገዛ የክልሉ ሕዝብ የማያውቀው አዲስ ባህል በመጎልበቱ ይህንንም እንደሚዋጉት መናገራቸውን ገልጿል። ‹‹እሳት ያልፈራ ሕዝብ እናንተን የሚፈራ ይመስላችኋል?›› ሲሉም ጥያቄ አቅርበዋል። ” መተካካት ወደ መገፋፋት በመቀየሩ ያለ ዕድሜና አቅም ማነስ ዶ/ር አርከበና አምባሳደር ብርሃነ እንዲወጡ መደረጉ እንዲሁም እንደ ድሮው መገማገምና አንዱ አንዱን ተጠያቂ ማድረግ በመሸፋፈንና በመጠባበቅ መቀየሩም በጉባኤው ላይ መነሳቱን ጋዜጣው ዘግቧል።

Source:: Ethsat

የቀድሞዋ የአባይ ጸሐዬ ሚስት ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር /ሞንጆሪኖ/

አቶ መለስ ዜናዊ በሕይወት በነበሩበት ዘመን የካሳንቺሱን መንግስት ከመቀሌ አምጥተው የደባለቋት ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር /ሞንጆሪኖ/ በንትርክ ላይ ባለው የሕወሓት ጉባኤ ላይ ነጥረው ወጥተዋል:: ዛሬ ወይም ነገ የሕዝብ ድምጽ ይሰጥበታል በሚባለው በዚሁ ጉባኤ ላይ አቶ መለስ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አድርጎ ያመጣት ሞንጆሪኖ ለትልቅ ቦታ ታጭታለች እየተባለ ነው:: ለመሆኑ ይህች ሴት ማናት?

ኤርሚያስ ለገሰ የመለስ ትርፉቶች በሚለው መጽሐፉ ላይ እንዲህ ጽፏት ነበር:: ተጨማሪ መረጃዎች እስኪመጡ መልካም ንባብ::

የሞንጆሪኖ ለቅሶ…

በሰፈሩት ቁና ሆነና ነገሩ የሕወሓት መሰንጠቅ የሞንጆሪኖን ፍጹማዊ አገዛዝ እንዲያከትም አደረገው:: በ እርግጥ የተስፈማሪያምን ያህል ውግዝ ከማርዮስ አልደረሰባትም:: ከአቶ መለስ ተግሳጽ ውጭ::

አቶ መለስ እንዲህ አላት:-

“ሞንጆሪኖ አዲስ አበባን የለውጥ ማዕበል ውስጥ አስገብተሽ ታስተካክያለሽ ብለን ነበር የላክንሽ:: አንቺ ግን የድርጅቱን አደራ በልተሽ ከጀርባ ስታደራጂ ከረምሽ:: ኸረ ለመሆኑ ምን ጎድሎብሽ ነው? እነስዬን ስታውቂያቸው ቀርተሽ ነው; አብረሽ ድርጅቱ ላይ ገመድ ልታጠልቂ የነበረው?”

ሞንጆሪኖ ተንሰቅስቃ አለቀሰች:: ስጋ ስው አትን ጠርታ ሁለተኛ እንደማይለመዳት ቃል ገባች:: እግሩ ላይ ተደፍታ ይቅርታ ጠየቀች:: ከነተወልደ ጋር እንዲኤት እንደተመሳጠረች ዘከዘከች:: የህቡዕ እንስቃሴው ከስድስት ወር በፊት በአዲሳባ መጀመሩን አስረዳች:: በአዲስ አበባ ያሉት የዞን ሊቀመናብርት ትልቁ ሥራቸው መሆኑን ገለጸች:: ካድሬዎቹ አባዝተው ስለበተኑት ወረቀት ዘከዘከች:: አመናት::

ፊቱን ወደ እሷ አነሳ… ራራላት::

እንደቀድሞ ባሏ አባይ ጸሐዬ የምህረቱ ተቋዳሽ አደረጋት:: የዘመናዊ ዕውቀት ማነስ የፈጠረው ችግር ሊሆን እንደሚችል በመግለጽ የቀለም ትምህርት እንድትማር ፈረንጅ ሃገር ሰደዳት:: ትምህርቷን አጠናቃ እንደመጣች ጓዟን ጠቅልላ መቀሌ ገባች:: የትግራይን ካቤኔ ተቀላቀለች:: ለአቶ መለስ ያላትን ታማኝነቷን በተግባር አሳየች:: እሱም ካሳውን በቁሙ ተቀበለ:: በዚህ ሳይወሰን በሕወሓት ሁለተኛ ትውልድ ውስጥ እንድትታቀፍ የመጀመሪያው ምርጫ አደረጋት::

(ሞንጆሪኖ ፈትለወርቅ ሆናለች:: የአዲሷ ፈትለ ወጣትነት የድሮዋ ሞንጆሪኖ ነው:: አፍታም ሳይቆይ የሕወሓት ድርጅታዊ ጉባኤ በመቀሌ ተካሄደ:: ፈትለወርቅ የሕወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ሆነች::

(የመለስ ትርፉቶች መጽሐፍ ገጽ 56 – 57)

***

Source:: Zehabesha

Wednesday, August 26, 2015

በአቶ ማሙሸት አማረ የሀሰትና የተጠና ክስ መቅረቡን ጠበቃው ተናገሩ


ነኅሴ ፳ (ሀያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም መንግስት በጠራው ሰልፍ ላይ ህዝብን አነሳስቷል በሚል ክስ የተመሰረተበት አቶ ማሙሸት አማረ ነሃሴ 20/2007 ዓ.ም አራዳ ምድብ ችሎት ቀርቦ ክሱን ተከታትቷል።
ከአራቱ ምስክሮች መካከል ሶስቱ ‹‹አቶ ማሙሸት አማረ 300 ብር ከፍሎ ሰልፍ እንድንወጣ አድርጎናል›› ሲሉ መስክረዋል፡፡
ይሁንና ምስክሮቹ ከማሙሸት ጋር በተገናኙበት ወቅት እንዲሁም ገንዘቡ ሲሰጣቸው፣ ሰልፉ ያለፈባቸውን ቦታዎችና ስለ ሌሎችም ጉዳዮች ሲጠየቁ ‹‹አላስታውሰውም›› ከማለት ባለፈ ዝርዝር የምስክርነት ቃል ሳይሰጡ መቅረታቸውን ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። ከምስክሮቹ መካከል ሁለቱ አቶ ማሙሸትን ያስያዙት ደህንነቶች መሆናቸውን አቶ ማሙሸትና ጠበቃው በችሎቱ የገለፁ ሲሆን፣ ምስክሮቹ በበኩላቸው ስራቸውን ሲጠየቁ ‹‹የግል›› እያሉ ከመመለስ ውጭ የመንግስት ስራ እንደማይሰሩ ተናግረዋል፡፡ ከሶስቱ ምስክሮች መካከል አንደኛው ስራውን ሲጠየቅ ‹‹የግል›› ብሎ የነበር ቢሆንም፣ በመስቀለኛ ጥያቄ የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ጥቃቅንና አነስተኛ አመራር መሆኑን አምኗል፡፡
ከምስክሮቹ መካከል ሁለቱ የመኢአድ ደጋፊዎች መሆናቸው ን ሲጠቅሱ፣ አንደኛው አቶ ማሙሸት ባቀረቡበት የመስቀለኛ ጥያቄ ከምርጫ በኋላ የወጣቶች ሊግና የኢህአዴግ አባል መሆኑን አምኗል ሲል ጋዜጣው ዘገቧል፡፡ የኢህአዴግ አባል ሆኖም ቢሆን መኢአድን እንደሚደግፍም ገልጾአል፡፡ ዳኛው ‹‹በሁለት ወር ውስጥ እንዴት ብለህ የወጣቶች ሊግ አባል መሆን ቻልክ?›› ብለው ሲጠይቁት ምስክሩ መመለስ ሳይችል ቀርቷል።
የአቶ ማሙሸት አማረ ጠበቃ በበኩላቸው ሶስቱም ምስክሮች አብዛኛዎቹን ጉዳዮች እንደማያስታውሱ በመግለፃቸው የተጠና የምስክርነት ቃል መሆኑን ለችሎቱ አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም ከ7 አመት በላይ አዲስ አበባ ውስጥ ኖረው መስቀል አደባባይን ጨምሮ ሰልፉ ተደረገባቸው የተባሉትን ቦታዎች አናውቃቸውም ማለታቸው፣ መተዳደሪያ ስራቸውን መደበቃቸውና መታወቂያ ለማሳየትም ፈቃደኛ አለመሆናቸው ምስክርነቱ የሀሰት እንደሆነ ስለሚያረጋግጥ ደንበኛቸው በነፃ እንዲለቀቁ ጠይቀዋል፡፡

ኢትዮጵያዊው ነጋዴ በደቡብ ሱዳን ተገደለ


ነኅሴ ፳ (ሀያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ሱዳንዋ ዋና ከተማ ጁባ ማንነቱ ባልታወቀ ነፍጥ ባነገተ ታጣቂ ግለሰብ በተተኮሰ ጥይት አንድ ኢትዮጵያዊ ነጋዴ ሲገደል ሌሎች ደግሞ ክፉኛ ቆስለዋል። ማክሰኞ ዕረፋዱ ላይ በጁባ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጽሕፈት ቤት ደጅ ላይ ዳቦ በመሸጥ ይተዳደሩ የነበሩት ኢትዮጵያዊያን ነጋዴዎችን የገደለውና ያቆሰለው ግለሰብ እስካሁን አልተያዘም።
የአካባቢው ነዋሪዎች የሩምታ ተኩሱን ተከትሎ እንቅስቃሴያቸው የተገታ መሆኑንና ከቤት አለመውጣቸውን የአካባቢው የወጣቶች ተጠሪ ማጆር ዬን ለራዲዮ ታማዙጅ ገልፀዋል።
የጁባ ሆስፒታል የድንገተኛ ክፍል ኃላፊ ዶክተር አብርሃም አደልት ፣ አንድ ሕጻንን ጨምሮ ሦስት ሰዎች ቆስለው ወደ ሕክምና ማዕከሉ ከመጡ በሁዋላ አንዱ ህይወቱ ወዲያውኑ ማለፉን ገልጸዋል።ሌሎቹ ሁለት ቁስለኞች በሆስፒታሉ ውስጥ ተኝተው ሕክምናቸውን እየተከታተሉ ነው።በደቡብ ሱዳን ስርዓት አልበኝነትና ወንጀሎች በከፍተኛ ሁኔታ እየተባባሱ መምጣታቸውን ራዲዮ ታማዙጅ አክሎ ዘግቧል።

Tuesday, August 25, 2015

Despite border crackdown in Ethiopia, migrants still risk lives to leave

The mood in the border town of Metema these days is quiet and watchful.
Dozens of houses on the hot, dusty main road that stretches from Ethiopia into Sudan look as if they have been closed in haste. Guards grimly patrol the border, stopping anyone who looks as if they are trying to cross illegally. The nightclubs and bars are emptier than usual, although they still attract Sudanese who cannot drink alcohol in their own country under sharia law.
Metema, with a population of some 100,000 people, is one of a handful of towns across the region that serve as feeders for a booming trade in migrants from Ethiopia, Eritrea, Somalia and Sudan, with many hoping to make their way to Europe. Life has become a cat-and-mouse game: the authorities are cracking down, yet the migrants just keep coming, often risking death.
Since 30 Ethiopian Christians who passed through Metema were killed by the Islamic State (Isis) group in Libya a few months ago, the Ethiopian government has become much more vigilant. It claims to have detained 200 smugglers across the country, and police say about 28 of them are from Metema.
In Metema, the effect of the crackdown is clear. But while the flow of migrants has dropped from about 250 a day, it’s still strong at 100 to 150, according to Teshome Agmas, the mayor. “It’s just a pity that people choose to endanger their lives in an effort to move out of their country and work in inhumane conditions abroad,” he said.
Getachew Merah, a 30-year-old migrant from Ethiopia, stands by a tree near Metema, on 4 June 2015.
Pinterest
 Getachew Merah, a 30-year-old migrant from Ethiopia, stands by a tree near Metema, June 2015. Photograph: Mulugeta Ayene/AP
Getachew Merah, a rail-thin 30-year-old aspiring migrant from Ethiopia, has made three unsuccessful attempts to cross into Sudan, and is now trying again. He said his father is dead and his mother lives in extreme poverty in a rural village in the Amhara region.
Merah has tried just about every job in Ethiopia. He’s worked as a butcher, a guard, an assistant in a heavy-duty truck, a labourer carrying oil back and forth from between Sudan and Ethiopia and more. But he simply can’t get enough money to change his life or his family’s. He hopes to earn money in Libya to send back to his family, and eventually return to start his own business.
Three times before, Sudanese police arrested him and sent him back to Ethiopia. Each time, he didn’t have enough money in his pocket to bribe the police. So this time, he is planning to enter Sudan as a daily labourer on a farm and earn about $150 – enough for bribes – and then disappear into the forest to reach the capital, Khartoum.
“I’m tired of working in Ethiopia,” said Merah. “I know the dangers of living now in Libya, especially with the Isis news. But I want to risk it all and try my luck.”
Almost 80% of Metema’s businesses are run by smugglers and their affiliates, according to Sister Hamelmal Melaku of the Ethiopia Higher Clinic. They smuggle charcoal, oil, fruit and, of course, people. With the government sweep-out, migrants are no longer showing up at the clinic, and the temporary shelter built for migrants in the middle of the town sits idle.
“I think it won’t be an exaggeration if I say that the town is totally out of the government’s control,” she said.
With Metema under surveillance, the smugglers are now changing their tactics, according to Abraraw Abeje, police assistant inspector. He said they are now “dumping” the migrants in forests and mountainous areas, and then forcing them to resume their journey into Sudan on foot or in packed vehicles.
Like the migrants, the suspected smugglers say they are poor. Adamo Anshebo is under detention in Metema as a suspected kingpin, which he denies. “I came here after selling all my property to receive and take back home my sick child, who was working in Sudan,” he said. There is no way to tell if it is the truth.
Prisoners look out at Adamo Anshebo, right, who is being held as an alleged kingpin, as he walks through the detention centre in Metema. He denies trafficking charges.
FacebookTwittePinterest
 Prisoners look out at Adamo Anshebo, right, who is being held as an alleged smuggling kingpin, as he walks through the detention centre in Metema. He denies trafficking charges. Photograph: Mulugeta Ayene/AP
Poverty in Ethiopia fell significantly from 44% in 2000 to 30% more than a decade later, according to the World Bank. However, the country remains one of the world’s poorest and is ruled by an authoritarian government. More than 96% of people in the country’s rural areas are still barely eking out a living, according to Oxford University’s poverty index.
Ethiopia is also a transit point for most Eritreans travelling to Europe, according to the UN’s high commissioner for refugees. While exact numbers vary, Eritreans make up one of the largest groups of migrants crossing the Mediterranean, coming second in number only to Syrians. Somalis are third.
According to accounts from several migrants and officials, the smugglers operate in and from all parts of Ethiopia. While major smugglers stay in cities like Addis Ababa, the capital, affiliates known as “shaqabas” operate in and around small towns like Metema, Moyale to the south and Afar in the north-east.
The migrants say they are not asked for money in Metema, because they could easily be robbed or lose it. Instead, they are charged upon arrival in Khartoum or other Sudanese cities. The final payment is made once they reach the Libyan coast and, in many cases, depart for Europe. The trip to Europe can cost as much as $5,000. Often, the migrants don’t carry all their money for fear of being robbed, so payment is made through their families, via transfer by hand to the smugglers or affiliates in their hometowns.
Metema’s government officials said they have repatriated more than 1,100 migrants arrested while trying to cross to Sudan illegally. They come from all parts of Ethiopia, especially the south, as well as Eritrea, the officials said. Ethiopian immigration officials on the Sudan border confirm that some of the migrants are foreigners, and more now from South Sudan because of the conflict there.
Women sell food at the roadside in Metema, where a crackdown by authorities is failing to stem the tide of migrants trying to leave.
FacebookTwittePinterest
 Women sell food at the roadside in Metema, where a crackdown by authorities is failing to stem the tide of migrants trying to leave. Photograph: Mulugeta Ayene/AP
Other migrants tell similar stories of poverty. Two women in their 20s travelling together, who refused to give their names out of fear of their safety, said their only reason for migration is economic. They, too, said they wanted to work abroad, then return home to help their families and start a business. Both have not worked in Ethiopia since completing high school.
Another young man, Abinet Yirga, 23, said his job in a billboard advertising company in Addis Ababa did not even leave him with enough money to buy clothes. He said two years ago, he was out of work for many months, which led to a feud with his father. He is now in Metema waiting to cross the border.
“I don’t know when I will travel to Sudan and then to Libya to go to Europe, because I don’t have any money now,” he said. “But I’ve decided I have to change my life whatever the cost is, even if it means life or death.”