"Democracy must be built through open societies that share information" Atifete Jahjaga
Press Freedom, Democracy and Human right
Friday, March 24, 2017
Sunday, March 12, 2017
Wednesday, January 11, 2017
Monday, January 9, 2017
Wednesday, April 27, 2016
ዜጎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ወደ አዲስ አበባ መፍለሳቸውን ቀጥለዋል
በአዲስ አበባ ውስጥ በተናጠል የሚመጡና በልመና ላይ የተሰማሩ ዜጎችን ሁሉንም የእድሜ ክልልና ጾታዎች የሚያካትት ነው። የኢሳት ካነጋገራቸው ዜጎች ለመረዳት እንደሚቻለው ብዙዎቹ ተሰደው የመጡት ከአማራ ክልል ነው።
በሰሜን ሸዋ ዞን በደራ ወረዳ ነዋሪ የሆኑና በአዲስ አበባ በልመና ህይወታቸውን ለማቆየት የሚጥሩት እናት እንደተናገሩት፣ በአካባቢያቸው የገባው ረሃብ ከፍተኛ በመሆኑ በሰውና በእንስሳት ላይ ጉዳት እያደረሰ ነው። መንግስት በቂ እርዳታ ለመስጠት ባለመቻሉ ወደ አዲስ አበባ ለመምጣት መገደዳቸውን ገልጸዋል
ከአዊ ዞን እንደመጡ የተናገሩት ሌላ እናት በበኩላቸው፣ ችግሩ ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ፣ ወደ አዲስ አበባ መጥተው ለመለመን መገደዳቸውን ተናግረዋል።
የማዳበሪያ እዳ አስመርሯቸው መምጣታቸውን የሚናገሩት አንድ አዛውንት፣ ለምነው በሚያገኙት ገንዘብ እዳቸውን ለመክፈል ማሰባቸውን ይገልጻሉ
የሚጦሩዋቸው ልጆች በማጣታቸው ወደ አዲስ አበባ እንደመጡ የሚናገሩ ሌላ አዛውንት፣ በአዲስ አበባ ህዝቡ ምጽዋት እየሰጠ እያኖራቸው መሆኑን ተናግረዋል
የውጭ ምንዛሪ ያስገኛሉ ተብለው በመንግስት ድጋፍ ሲደረግላቸው የቆዩ ኩባንያዎች ውጤታማ አይደሉም ተባሉ
Tuesday, April 26, 2016
ሃረር ከቤት ፈረሳ ጋር በተያያዘ ተወጥራ ዋለች
በሸንኮር መስተዳደር ስር በሚገኙ አካባቢዎች 1 ሺ ያላነሱ ቤቶች እንደሚፈርሱ የገለጸው ወኪላችን ፣ ዛሬ ሸንኮር መስተዳድራና በድሬ ጥያራ መለያ ቦታ ላይ በሚገኘው ድልድይ ላይ ነዋሪዎች ቋጥኝ ድንጋይ እያንከባለሉ መንገዶችን የዘጉ ሲሆን፣ ይህን አልፎ በሚመጣ ላይ እርምጃ እንወስዳለን በማለት በመናገር ላይ ናቸው።
ቤቶቹ የሚፈርሱት በሸንኮር ወረዳ፣ ከአቡበክር ወረዳ፣ ከሃኪም ወረዳ እንዲሁም ከሶፊ ወረዳ ናቸው። ጊዮርጊስ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ቤት አፍራሽ ግብረሃይል ቤት ማፍረስ የጀመረ ሲሆን፣ ህዝቡ ቀኑን ሙሉ በጩከት ተቃውሞውን ሲገልጽ ውሎአል። አንድ አዛውንት የጎረቤታቸው ቤት ሲፈርስ አይተው በድንጋጤ ህይወታቸው ማለፉ ታውቋል።
ቤቶቻቸው የሚፈርሱባቸው ሰዎች በየአመቱ ግብር ይገብሩ እንደነበር ነዋሪዎች በማነጋገር ወኪላችን ከላከው መረጃ ለመረዳት ይቻላል።
Monday, April 11, 2016
በአፋርና በኢሳ ጎሳዎች መካከል ግጭት ተቀስቅሶ በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ
Wednesday, April 6, 2016
በህገወጥ ንግድ ተሰማርታችኋል የተባሉ ነጋዴዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
ድርቅ የተባባሰባቸው 438 ወረዳዎች አሳሳቢ ደረጃ ላይ ናቸው ተባለ
በመከላከያ ውስጥ የሚገኙ የትግራይ ተወላጆች ብቻ የትግራይ ህዝብ ተጋድሎ ለሚያሳየው ፊልምና መጽሃፍ ገንዘብ እንዲያዋጡ ተጠየቁ
የድምጽና ምስል ግንኙነት የሚሰጡ አገልግሎቶች ላይ ክፍያ ለመጣል እየተመከረበት እንድሆነ ኢትዮ-ቴሌኮም አስታወቀ
Sunday, January 17, 2016
በሰርጉ ዋዜማ በጥይት የተመታው መምህር ፍጹም አባተ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ቀዶ ጥገና ተደረገለት
ኢሳት (ታህሳስ 5 2008)
በኢሊባቡር መቱ በሰርጉ ዋዜማ በጥይት የተመታው መምህር ፍጹም አባተ ህይወቱ አስጊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ከቤተሰቦቹ የተገኘው መረጃ አመለከተ።
ታህሳስ 29 ቀን 2008 ዓ ም ጭንቅላቱን በጥይት የተመታው መምህር ፍጹም፣ በመቱ ሆስፒታል ከታየ በኋላ ለከፍተኛ ቀዶ ጥገና ሕክምና ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከዚያም ወደ ወደአለርት ሆስፒታል ተልኮ የነበረ ሲሆን በመጨረሻም ወደ ጥቁር አንበሳ ተመልሶ ቀዶ ጥገና እንደተደረገለት ለማወቅ ተችሏል።
በጥቁር አንበሳ በዛሬው እለት ቀዶ ጥገና የተደረገለት ፍጹም አባተ፣ የማየት እድሉ ከ 5-10 ፐርሰንት እንደሆነ ቀዶ ጥገናውን ያደረጉ ሃኪሞች መናገራቸው ታውቋል።
ጭቅላቱን በጆሮ በኩል በኋላ የተመታው መምህር ፍጹም፣ ቀዶ ጥገና ከተደረገለት በኋላም ቢሆን ብዙ መናገር እንደማይችል ቤተሰቦቹ ለኢሳት አስረድተዋል።
በሙሽራው ላይ የተኮሱት የመንግስት ወታደሮችም በህግ ቁጥጥር ስር ላይ ናቸው እንደተባሉ የሙሽራው አባት አቶ አባተ ለኢሳት ገልጸዋል። ወታደሮችም ለምን ይህንን አይነት የጭካኔ እርምጃ እንደወሰዱ የሚታወቅ ነገር የለም ተብሏል።
የቤተሰቡ ሶስተኛ ልጅ የሆነውና ለ8 ዓመት በመምህርነት ያገለገለው ፍጹም አባተ፣ አጥንቱ ከመሰበሩም በተጨማሪ፣ ደም ወደውስጥ እንደፈሰሰበትም ወላጅ አባቱ አቶ አባተ ለኢሳት ገልጸዋል።
“በልጄ ላይ ደረሰው አደጋ በማንም ላይ እንዳይደርስ እፈልጋለሁ” ያሉት የመምህር ፍጹም አባት አቶ አባተ፣ የህክምናውን ወጪ የሚሸፍኑት በእድሜ የገፉ የፍጹም አባትና ቤተሰቦቻቸው እንደሆኑ ለኢሳት ተናግረዋል።
የመምህር ፍጹም እጮኛ ወ/ሪት ፍሬህወት በበኩሏ አደጋው እጅግ በጣም አስደንጋጭ ሁኔታ እንደፈጠረባት ለኢሳት ገልጻለች።
ሰለአደጋው በስልክ ከሙሽራው እህት እንደተደወላት የተናገረችው ወ/ሪት ፍሬህወይት፣ መኪና ተፈልጎ ከበቹ ወደ ቡሪሳ ሌሊት እንደመጣችና ተጎጂ እጮኛዋን ማየት እንደቻለች አስረድታለች።
ወ/ሪት ፍሬህይወት በለጠ የኢትዮጵያ ህዝብም ጸሎት እንዲያደርግ ጠይቃለች።
መምህር ፍጹም፣ በስራው እጅግ የተከበረና በተማሪዎች ዘንድም በጣም ተወዳጅ እንደሆነ የተለያዩ ሰዎች መስክረዋል።
Source:: Ethsat
በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው
ኢሳት (ጥር 6 ፥ 2008)
በኦሮሚያ ክልል ዳግሞ ቀጥሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ተቃውሞ አርብ በምስራቅ ሃረርጌ እንዲሁም በምዕራብ ሸዋ የኦሮሚያ አካባቢዎች ሲካሄድ መዋሉን ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል።
በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎችና ተማሪዎች የጸጥታ ሃይሎች እየወሰዱ ያለውን እርምጃ በማውገዝ የተቃውሞ መልዕክቶችን ማስተላለፋቸውን ታዉቋል።
ይሁንና የጸጥታ ሃይሎች ተቃውሞውን ለመበተን በወሰዱት እርምጃ በርካታ ተማሪዎች ለእስር የተዳረጉ ሲሆን ተመሳሳይ ተቃውሞም በምዕራብ ወለጋ አካባቢ መካሄዱን ለመረዳት ተችሏል።
የአምቦ ዩንቨርስቲን ጨምሮ በዲላና በሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የትምህርት ማስተማሩ ሂደት አሁንም እንደተቋረጠ ተማሪዎች አስታውቀዋል።
ዩንቨርስቲዎቹ ተማሪዎች ወደትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ ማሳሰቢያ ቢያወጡም ትምህርት አለመጀመሩን ተማሪዎች አክለው ገልጸዋል።
ትምህርታቸውን አቋርጠው የሚገኙ ተማሪዎች ለእስር ተዳርገው የሚገኙ ተማሪዎች እንዲፈቱና የጸጥታ ሃይሎች የሚወስዱትን የሃይል እርምጃ እንዲያቆሙ ጠይቀዋል።
በዩንቨርስቲዎቹ ሰፍረው የሚገኙ የጸጥታ ሃይሎች ለደህንነታቸው ስጋት ኣንደሆኑባቸው የሚገልጹት እነዚሁ ተማሪዎች፣ ጥያቄያቸው ምላሽ ካላገኘ ትምህርታቸውን እንደማይቀጥሉ ገልጸዋል።
Source:: Ethsat
Thursday, January 14, 2016
በአዲስ አበባ ካለምንም ቅድመ ማስጠንቀቂያ የመንገድ ዳር ንብረቶች መወረሳቸው ተዘገበ
ጥር ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የከተማዋ የመንገድ ባለስልጣን መስሪያ ቤት በመንገዶች ዳርቻ ያሉ ዓመታዊ ግብር ተከፍሎባቸው የቆሙ ቢልቦርድ የንግድ ማስታወቂያዎችን ለድርጅቶቹ ምንም ዓይነት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ተለዋጭ ቦታ ሳይሰጣቸው ሳይሰጣቸው ከተለጠፉበት ማንሳቱን ሸገር ኤፍ ኤም ዘግቧል። ንብረታቸው የተወሰደባቸው የከተማዋ ነዋሪዎች እንደዚህ ዓይነት ሕገወጥ ድርጊት በሕግ ሽፋን መፈፀሙ እንዳስከፋቸው እየገለፁ ነው። የመንገድ ባለስልጣኑ በበኩሉ በሬድዮ ለሶስት ቀናት ማስታወቂያ አስነግሬያለሁ በማለት ማስተባበያ ሰጥተዋል።
Source: http://ethsat.com/amharic/%e1%89%a0%e1%8a%a0%e1%8b%b2%e1%88%b5-%e1%8a%a0%e1%89%a0%e1%89%a3-%e1%8a%ab%e1%88%88%e1%88%9d%e1%8a%95%e1%88%9d-%e1%89%85%e1%8b%b5%e1%88%98-%e1%88%9b%e1%88%b5%e1%8c%a0%e1%8a%95%e1%89%80%e1%89%82/
Thursday, January 7, 2016
ሱፊ ቱራ አዳም ይባላል። ትናንት ከሂርና ከተማ በኢህአዴግ ታጣቂዎች ታስሮ ከሌሎች ጋር ወደአዲስ አበባ እየተወሰደ ሳለ በደረሰበት ድብደባ ወታደሮች የሞተ መስሏቸው ከመኪናው ላይ ወርውረው ጥሻ ውስጥ ጣሉት።
Source:https://www.facebook.com/photo.php?fbid=10207203607360555&set=a.3052522444099.2136911.1594431019&type=3&permPage=1
ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት መከሰቱን ነጋዴዎች ተናገሩ
በአገሪቱ የተፈጠረውን ከፍተኛ ድርቅ ለማቋቋም መንግስት በአለም ባንክ የገንዘብ ድጋፍ የእርዳታ እህል ለመግዛት ቢችልም፣ ከአለማቀፉ ማህበረሰብ የሚሰጠው ድጋፍ በመቀነሱ ተጨማሪ የእርዳታ እህል ለመግዛት አቅም አጥሮታል። ከዚህ ቀደም የተከሰተውን የዶላር እጥረት ለመቋቋም መንግስት ከአለማቀፍ የግል አበዳሪ ድርጅቶች 1 ቢሊዮን ዶላር ቢበደርም ፣ ሁለተኛው ዙር ብድር እስካሁን አለመለቀቁ ችግሩን አባብሶታል ሲሉ ምንጮች ይገልጻሉ።
በባህርዳር እስረኞች ለ2 ቀናት በቤተሰብ እንዳይጠየቁ ተደረጉ
ዛሬ ታህሳስ 28 ከቀኑ 8 ሰአት ላይ እስረኞችን ለመጠየቅ መግባት እንደተጀመረ ድንገተኛ የተኩስ ድምጽ በመሰማቱ፣ ወታደሮች ጠያቂ ቤተሰቦችን ከአካባቢው በማባረር የተወሰኑትን አግደዋል።
የተኩሱ ትክክለኛ መንስኤ እስካሁን ባይታወቅም ፣ አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የጠየቀ ፖሊስ ግን በጣና ሃይቅ በኩል ለማምለጥ የሞከረን እስረኛ ለማስቆም በሚል ተኩስ መከፈቱን ለዘጋቢያችን ተናግሯል።
በባህርዳር ዋናው እስር ቤት መንግስትን ይቃወማሉ የሚባሉ በርካታ ወጣቶች ታስረው ይገኛሉ።
በትግራይ አርሶአደሮች የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ
አርሶአደሮቹ እንደሚሉት ለምርምር በሚል የገባው በሽታ ፣ የበለስ ምርቱን በከፍተኛ ሁኔታ በመጉዳቱ በህልውናቸው ላይ አደጋ ፈጥሯል። መንግስት በሽታውን ያመጡትን ተመራማሪዎች ለፍርድ እንዲያቀርብላቸውና አስፈላጊው ካሳ እንዲፈላቸው ይጠይቃሉ።
የክልሉ መንግስት ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ጥያቄ ባቀረቡ አርሶአደሮች ላይ የሃይል እርምጃ መውሰዱ ይታወቃል።
የኣብረሃ ደስታ ወንድም ታሰረ።
ዛሬ ሓሙስ 28 / 04/ 2008 ዓ/ም ለልደት በዓል ወንድማቸው ኣብራሃ ደስታ ለመጠየቅ ወደ ቃሊቲ ማረምያቤት ያመሩ ተወልደ ደስታና ገብረሂወት ደስታ የወህኒ ቤቱ ሃላፊዎች ለገብረሂወት ኣብራሃን እንዲጠይቅ የፈቀዱለት ሲሆኑ ተወልደን ግን ይዘውት ወዳልታወቀ ቦታ ወስደውታል።
ገብረሂወት ወንድሙ ኣብራሃን ጠይቆ ሲመለስ ተወልደ እንዳጣውና የት እንዳስገቡት ሲጠይቃቸው ኣናውቅም እንዳሉት ገልፆልኛል።
በነገራችን ላይ እነአብርሃ ደስታ ነገ 29/04/2008ዓ/ም ኣምስት ኪሎ በሚገኘው ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለብይን ይቀርባሉ።
ነፃነታችን በእጃችን ነው።
It Is So.
Source: https://m.facebook.com/photo.php?fbid=964990906925899&id=100002449960026&set=a.881616671929990.1073741831.100002449960026&source=57