Thursday, January 7, 2016

የኣብረሃ ደስታ ወንድም ታሰረ።

ዛሬ ሓሙስ 28 / 04/ 2008 ዓ/ም ለልደት በዓል ወንድማቸው ኣብራሃ ደስታ ለመጠየቅ ወደ ቃሊቲ ማረምያቤት ያመሩ ተወልደ ደስታና ገብረሂወት ደስታ የወህኒ ቤቱ ሃላፊዎች ለገብረሂወት ኣብራሃን እንዲጠይቅ የፈቀዱለት ሲሆኑ ተወልደን ግን ይዘውት ወዳልታወቀ ቦታ ወስደውታል።

ገብረሂወት ወንድሙ ኣብራሃን ጠይቆ ሲመለስ ተወልደ እንዳጣውና የት እንዳስገቡት ሲጠይቃቸው ኣናውቅም እንዳሉት ገልፆልኛል።

በነገራችን ላይ እነአብርሃ ደስታ ነገ 29/04/2008ዓ/ም ኣምስት ኪሎ በሚገኘው ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለብይን ይቀርባሉ።

ነፃነታችን በእጃችን ነው።
It Is So.




Source: https://m.facebook.com/photo.php?fbid=964990906925899&id=100002449960026&set=a.881616671929990.1073741831.100002449960026&source=57


No comments:

Post a Comment