Wednesday, May 6, 2015

ባለሃብቶች መስራት አልቻንልም አሉ


ሚያዝያ ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ” የኢንዱስትሪውን  ልማት በተሳለጠ መንገድ ይዘን በመጓዝ የአምስት አመቱን ዕቅድ ለማጠናቀቅ  በስኬት ጎዳና ላይ ነኝ ” በሚል  የገዢው መንግስት ቢናገርም፤ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሃብቶች በርካታ ችግር
እየገጠማቸው መሆኑን ተናገሩ፡፡
ሰሞኑን በተካሄደው የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ ባለስልጣናት  ከከፍተኛ ባለሃብቶች ጋር ባደረጉት የውይይት መድረክ ላይ ፣ ባለሃብቶች  እንደገለጹት በባለስልጣናት ላይ የሚታየው የፍርሃት መንፈስ ስራዎች በታሰበላቸው ጊዜ እንዳይጠናቀቁ አድርጓል፡፡
ችግሮች በየደረጃው እንዲፈቱ በማሰብ የገዥው መንግስት የቀየሰውን የአሰራር ፖሊሲ እንዲያስፈጽሙ የተቀመጡት አመራሮች በራሳቸው ተማምነው ውሳኔ ከመስጠት ይልቅ ሌሎችን የመጠበቅ እና ውሳኔ በቶሎ አለመስጠት በዘርፉ በመታየቱ ተገቢውን አገልግሎት
ማግኘት አለመቻላቸውን ባለሃብቶቹ ተናግረዋል፡፡
ቅሬታ አቅራቢ ባለሃብቶች በየጊዜው የሚደረጉ የአመራሮች ከቦታ በመነሳት በየጊዜው መቀያየር ከፍተኛ ችግር እየፈጠረባቸው መሆኑን ተናግረዋል፡፡የስርአቱን ብልሹነት በሚያሳይ መልኩ በሙስናና በመልካም አስተዳደር ችግሮች ስድስት ወር ሳይሞላቸው የሚነሱ
አመራሮች ባሉበት ቢሮ ከውጭ ሃገር በመምጣት መዋእለ ነዋያቸውን የሚፈሱ የውጭ ሃገር ዜጎች ሃገራቸው ቆይተው በሚመጡ ጊዜ አመራሮች ተቀያይረው  ማግኘታቸው ጉዳያቸውን እንደ አዲስ ለማስረዳት በየጊዜው መቸገራቸው አንዱ ሲሆን አዲስ የሚመደቡት
አመራሮችም ጉዳዩን እናጥናው በማለት ተጨማሪ ጊዜ መውሰዳቸው ትልቅ ድካም ከማስከተሉም በላይ የውጭ ሃገር ዜጎች በገዥው መንግስት አሰራር ላይ ሁልጊዜ ጥርጣሬ እንዲያድርባቸው የሚያደርግ ክስተት መፈጠሩን ባለሃብቶቹ ተናግረዋል፡፡
‹‹ በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቅ ችግር በመሆን ላይ ያለው የምርት ጥራት ነው ፡፡ባለሃብቶች በክልሉ ውስጥ መዋዕለ ነዋያቸውን በማፍሰስ ቢያመርቱም፤ጎን ለጎን ጥራታቸውን ያልጠበቁ ተመሳሳይ ምርቶችን በማስገባትና በማቅረብ ኢንቨስተሩን ለኪሳራ የሚዳርግ አሰራር
በጉልህ ይታያል፡፡ ›› በማለት የሚናገሩት ሌላው ቅሬታ አቅራቢ በተለይ ጉዳዩን እንዲቆጣጠር የተመደበው የደረጃ መዳቢዎች ባለሥልጣን መስሪያ ቤት ሲሰራ የሚታየው ማህተም ማዘጋጀትና የዕውቅና ደብዳቤ መስጠት  ብቻ መሆኑ ገልጸዋል፡፡ባለስልጣን መስሪያቤቱ
አሰራሩ አግባብ እንዳልሆነ ጥራት እና ቁጥጥር ላይ ሳያተኩር በግዴለሽነት እየተመራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሆቴል ንግድ የተሰማሩ ባለሃብቶች ለአሰራራቸው ከፍተኛ ማነቆ በመሆን ያስቸገራቸውን አሰራር ሲገልጹ ደረጃቸውን በጠበቁ ሆቴሎች ህጋዊ የገቢ አሰባሰብ በመዘርጋት በዘመናዊ መልኩ እየሰሩ ቢሆንም ፤የገዢወው መንግስት ሹመኞች  የሚጠይቋቸው የግብር መጠን
በግምት ላይ የተመሰረተ መሆኑ ስራቸውን አደጋ ላይ መጣሉን ተናግረዋል፡፡በጎንደር የጃንተከል ሆቴል ባለቤት አቶ ተመስገን ሰጥአድርገው ሲናገሩ  የሽያጭ ማሽን ተገጥሞ በሚሰራባቸው ታላላቅ ሆቴሎች ከደንበኞች የሚሰበሰበውን ገቢ በአግባቡ ቢይዙም  መንግስት
ባለሃብቶችን ባለማመን በግምት በሚጥለው ግብር በመማረር ስራውን ለመተው ጫፍ መድረሳቸውን በምሬት ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡
በምእራብ አርማጮሆና መተማ አካባቢ በጥጥ ምርት ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች ባቀረቡት ቅሬታ በአካባቢው የሚመረተው ምርት ጥራቱን የጠበቀ ሆኖ እያለ በዘርፉ የተሰማሩ የውጭ ሃገር ባለሃብቶች በሃገራችን ለተከሉት ፋብሪካ ምርታቸውን ከውጭ ለማስገባት የሚያደርጉትን የተንኮል አሰራር የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት እንደሚያግዙዋቸው ሲናገሩ፤
የጥጥ ምርት በኢትዮጵያ በሚደርስበት ጊዜ በመጋዝናቸው ምርት እንዲኖር ፣በሃገር ውስጥ የነበረው ምርት ከባከነና በርካሽ ከተሸጠ በኋላ ‘ምርት እንፈልጋለን ‘ በማለት ከውጭ ሃገር የራሳቸውን ምርት በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንዲያስገቡ በማድረግ  ሀገሪቱ   የምታገኘውን
ጥቅም በማባከን ላይ መሆናቸውን በምሬት ሲናገሩ ተሰምተዋል፡፡ያመረቱትን ከፍተኛ ምርት በርካሽ  እንዲሸጡ የተገደዱት ባለሃብቶች እንባ አውጥተው በየስብሰባው የሚያለቅሱበት ጊዜ ላይ የደረሱ ቢሆንም ከፍተኛ ባለስልጣናት ምንም አይነት እርምጃ ባለመውሰዳቸው የባለሃብቶች ህልውና አደጋ ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
“በሰሊጥ ምርት የጥራት ደረጃ ማውጣትና ማወዳደር የሚገባው የምርት ገበያ ድርጅት ባለሃብቶች ያለሙያቸው  ለምርታቸውን ደረጃ በማውጣት ምርታቸውን እንዲያቀርቡ  በማስገደድ ያለአግባብ በመቅጣት እየበደለን ነው፡፡
” የሚሉት ባለሃብቶች፤ይህንንም ለከፍተኛ አመራሮች አቤት ቢሉም ቅጣቱን እንዳጸደቁባቸው ተናግረዋል፡፡መፍትሄ በማጣታቸውም ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት ለመውሰድ እንደተገደዱ ሲገልጹ ተሰምተዋል፡፡በሰሊጥ ምርት ለተሰማሩ ባለሃብቶችም ሆነ ለዘርፉ
የገዥው መንግስት ምንም ዓይነት ማበረታቻ  ባለማድረጉ ዘርፉ በጥቂት ሰዎች እጅ መያዙን ተናግረዋል፡፡
‹‹ጉዳይ ለማስፈጸም በክልል ደረጃም ብቃት ያለው ባለስልጣን የለም፡፡›› የሚሉት ባለ ሃብቶች ‘አንድ ደብዳቤ ጽፎ ይህ ይፈጸም! ‘ለማለት የሚችል አመራር በክልል ደረጃ አለመኖሩ በብድር አገልግሎት ለመጠቀም እንዳይችሉ ማድረጉን ገልጸው፤የውሳኔ አሰጣጥ ከጊዜ
ወደ ጊዜ እየባሰበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ባለሃብቶቹ በሁሉም ዘርፍ ከፍተኛ የቢሮክራሲ ጫና እየደረሰባቸው መሆኑን ገልጸው ፤ስርዓቱ የተለመደ የምርጫ ቅስቀሳ ላይ የሚናገረውን እውነታ በተግባር በማዋል ያለበትን ችግር ባለማስተካከሉ በዘርፉ ለመሰማራት አዳጋች መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ከአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ


Yilikal
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ትናንት ሚያዝያ 27/2007 ዓ.ም ከአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸውን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት የዴሞክራሲ፣ ሰብአዊ መብትና ሰራተኞች ምክትል ዋና ፀኃፊ የሆኑት ሚስተር ስቲቭ ፌልድስቴይን ጨምሮ ሌሎችንም ኃላፊዎች አግኝተው ስለ ኢትዮጵያና ስለ ቀጠናው ሰፋ ያለ ውይይት አድርገዋል፡፡
ኢ/ር ይልቃል ከስቴት ዲፓርትመንት ኃላፊዎቹ ጋር በነበራቸው ቆይታ ስለ መጭው ምርጫ፣ ሰብአዊ መብት አያያዝ፣ የእምነት እና ሀሳብን በነፃነት መግለጽ መብት፣ ሲቪክ ማህበረሰብ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በፀረ ሽብር ህጉና በደህንነት ስም እየተፈፀሙ ያሉ ችግሮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡
ሚስተር ፌልድስቴይን ስለ ሰማያዊ ፓርቲ እንቅስቃሴዎች ዝርዝር ጥያቄዎችን ያነሱ ሲሆን ኢ/ር ይልቃልም በዝርዝር ማስረዳታቸው ታውቋል፡፡ በቅርቡ ምክትል የውጭ ጉዳይ ኃላፊዋ ውይንዲ ሸርማን ንግግር ላይም መወያየታቸው ታውቋል፡፡

በቅርቡ በተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የታሰሩት ወጣቶች በሃሰት እንዲመሰክሩ ጫና እየተደረገባቸው ነው


ሚያዝያ ፳፯ (ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሊቢያና ደቡብ አፍሪካ በግፍ የተገደሉ ኢትዮጵያውያንን ለመዘከርና ቁጣቸውን ለመግለጽ ገዢው ፓርቲ በጠራው ሰልፍ ላይ የተገኙ ወጣቶች መንግስትን ሰድባችሁዋል በሚል ታፍሰው ከታሰሩ በሁዋላ፣ “ተቃውሞውን
ያስነሱት በእስር ላይ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ናቸው” ብላችሁ ካልመሰከራችሁ አትለቀቁም መባላቸውን የእስረኞች ቤተሰቦች ገልጸዋል።
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ቤተሰቦች ለኢሳት እንደተናገሩት፣ ወጣቶች ማታ ማታ በደህንነት ሃይሎች እየተጠሩ በታሰሩ የሰማያዊ አባላት ላይ እንዲመሰክሩ ጫና እየተደረገባቸው ነው።
ወላጆች ልጆቻቸው በንጹሃን ላይ በሃሰት እንዳይመሰክሩ እንደመከሩዋቸው ተናግረዋል። ህዝቡ በኑሮውና በፍትህ እጦት ተማሮ በራሱ ጊዜ ተቃውሞውን ቢያሰማም፣ ገዢው ፓርቲ ተቃውሞውን ያስነሳው ሰማያዊ ፓርቲ ነው በማለት እየወነጀለ ነው። የገዢውን ፓርቲ ውንጀላ
አባሎቹ ሳይቀሩ አልተቀበሉትም።

Elections, Ethiopian style


Since the last election, the ruling party has exerted more control and increased its repression of basic liberties.

There are few ways for Ethiopians to peacefully express dissent, writes Horne [Al Jazeera]


This is what an election campaign looks like in Ethiopia, where the ruling coalition took 99.6 percent of parliamentary seats in the last national elections, in 2010.
Jirata, who asked that his real name not be used, is a 19-year-old student who was campaigning for a legally registered opposition party recently, when security officials arrested him.
They told him that he was working for a "terrorist group" that sought to forcibly bring down the government. He was badly beaten over the course of three nights and released on the condition that he end his involvement in politics. He is still limping from his injuries, and he told me he no longer has any interest in getting involved in politics. He says he will vote for the government party "because life is easier that way".
Jirata was working for an Oromo party, representing an ethnic group long targeted by the government. But as Ethiopians go to the polls in late May, the prospects for opposition parties to fully and fairly campaign are grim.
Since the last election, the ruling party has only exerted more control and increased its widespread repression of basic liberties, including the rights to free expression, assembly, and association.
The courts provide no justice in cases of political importance. While election day is unpredictable, it's clear that the avenues by which opposition parties can fully function and citizens can engage on political issues are largely closed.
While there are 75 registered opposition groups, several of the largest parties have talked of boycotting the elections because of flawed electoral processes. Challenges with registering candidates, acquiring the funds they are legally entitled to, mobilising their supporters, and keeping their members out of prison have taken their toll.

Suppression of non-governmental voices
The Ethiopian media provides little coverage of relevant political issues ahead of the election since what vestiges of independent media existed have largely been eliminated since 2010.
Reporters critical of the government are regularly harassed, threatened and detained. In 2014 alone, over 30 journalists fled Ethiopia and at least six publications were closed down.
Sources providing information to media and human rights groups are regularly targeted. Many diaspora media websites, while heavily politicised, remain blocked in Ethiopia. Journalists must choose between self-censorship, harassment, imprisonment, and exile.
The situation hasn't been much better for opposition parties that want to organise peaceful protests and rallies ahead of the election. The Semayawi party (Blue Party), for example, is one of the newcomers in Ethiopia's electoral landscape, and since 2013 has tried to hold regular and peaceful issue-based protests.
Protesters and organisers have frequently been arrested and harassed, their equipment has been confiscated, and permits unfairly denied. One of their leaders is on trial on trumped-up terrorism charges.
The lone opposition parliament member is not running this time due to a split in his party, the Union of Democracy and Justice, in which Ethiopia's national electoral board played favourites. The net effect is that the government awarded the party name to an offshoot of the party that is more closely aligned to government policies and interests.

No dissent allowed
There are few ways for Ethiopians to peacefully express dissent or to contribute to the national political dialogue. Dissent of any type, particularly in rural areas, is dealt with harshly. The long-standing 5:1 system of grassroots surveillance - under which one individual is responsible for monitoring the activities of five households - has let local officials clamp down on dissent before it spreads beyond the household level.Telephone surveillance is commonplace, and the ongoing trial of a group of bloggers called Zone 9 has resulted in increased self-censorship online.
In short, there is limited space for government critics to play a peaceful and constructive role. The only international observers to the election will be the African Union. The European Union is not sending observers, noting that Ethiopia has not implemented recommendations by previous election observers. As Human Rights Watch documented after the 2010 elections, those who complain about election irregularities risk arrest and harassment.
"If we have an issue with government where do we go?" an Ethiopian who lives in a rural area recently told me, summing it up: "There is no media that will write our story, there are no more organisations that work on issues that the government does not like, if we take to the streets we are arrested, and if we go to their office to question we are called terrorists. If we go to the courts, there is no independence - we go to jail. There are no large opposition parties to vote for in the election, and even if there were, if we vote for them our lives then become very difficult. So what can we do? The elections are just another sign of our repression."

Tuesday, May 5, 2015

ምርጫ 2007 ምርጫ ሳይሆን ከፍተኛ ገንዘብ ማስገኛና የምዝበራ ቢዝነስ - ሚሊዮኖች ድምጽ








ለምርጫዉ ቅስቀስ ምርጫ ቦርድ ከመደበው ገንዘብ 15 ሚሊዮን ብር የሚሆን ለኢሕአዴግ ሲሰጥ፣ ለ 270 መቀመጫዎች ተወዳዳሪዎችን ላሰለፈው መድረክ፣ 2 ሚሊዮን ብር፣ ለ165 እና ለ139 መቀመጫዎች ተወዳዳሪዎች ላሰለፉት ኢዴፓና ሰማያዊ ወደ ስምንት መቶ ሺህ ብር የተመደበላቸው ተመድቦላቸዋል። ለትግስቱ አወሉ ቡድን ግማሽ ሚሊዮን ብር ተፈቅዶለታል።

አንድ የፓርላማ ተወዳዳሪ ብቻ ያሰለፉ ድርጅቶች ወደ አምሳ ሶስት ሺህ ብር ድጋፍ ከምርጫ ቦርድ አግኝተዋል ። ለምሳሌ የኢትዮጵያ ብሄራዊ አንድነት ፓርቲ እና የሶዶ ጎርዳና ህዝቦች ፓርት እያንዳንዳቸው አንድ የፓርላማ ተወዳዳሪ ብቻ ያሰለፉ ሲሆን ፣ እያንዳንዳቸው 53 790 ብር ተችረዋል። የመላው ኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ፓርቲ 2 ተወዳዳሪዎች ብቻ ሲያሰለፍ፣ ወደ 55875 ብር ተለግሰዋል።

የምርጫው ሂደት በርግጥ ትልቅ ዘረፋ የሚደረግበት፣ ፓርቲ በማቋቋም ጥቅም የሚገኝበት ቢዝነስ እንደሆነ፣ የምርጫ ቦርድ የገንዘብ ድጋፍ ቀመር በገሃድ ያመላከተበት ሁኔታ ነው።
ከአራባ ሰባት ለምርጫ ተወዳዳሪዎች ካሰለፉ ፓርቲዎች መካከል 83 በመቶ የሚሆኑት ስ9 ድርጅቶች ከ20 በታች ተወዳዳሪዎችን ነው ለፓርላም ያሰለፉት። ሃያ ሰባት ድርጅቶች ( 57% ) ከአሥር በታች፣ ሃያ ድርጅቶች ደግሞ (42% ) ከአምስት በታች ነው ለፓርላማ ተወዳዳሪዎች ያሰለፉት። ይሄም ብዙ ፓርቲዎች አሉ የሚባለው ከገዢው ፓርቲ የሚነዛው ፕሮፖጋንዳና መከርከሮያ ምን ያህል ባዶና እንደሆነ የሚያሳይ ነው።








Sunday, May 3, 2015

Police fire tear gas during demo against racism, police brutality in Tel Aviv (VIDEO)

Israelis take part in a demonstration in Tel Aviv called by members of the Ethiopian community against alleged police brutality and institutionalised discrimination, on May 3, 2015 (AFP Photo / Jack Guez)
Israelis take part in a demonstration in Tel Aviv called by members of the Ethiopian community against alleged police brutality and institutionalised discrimination, on May 3, 2015 (AFP Photo / Jack Guez)
Security forces have fired pepper spray, stun grenades during a protest against racism and police violence, staged by Jews of Ethiopian descent in Tel Aviv. Up to 20 policemen and one protester have been injured in the clashes.
Protesters tried to break into the City Hall, according to Haaretz, and at least three people have been arrested.





They shouted “not black, not white, we're all human beings” and “a violent cop should be jailed.”

“Being black, I have to protest today. I never experienced police violence against me personally, but it is aimed at my community which I have to support,” 34-year-old protester Eddie Maconen told AFP.





The demonstration started next to the key city artery Kaplan Interchange, with protesters blocking major junctions and surrounding streets. They also went up to the train station, but were cracked down on by police.
Two protesters have been detained, one of whom has already been released.

Brigade General Yoram Ohayon, deputy commander of the Tel Aviv police district, accused social activists and organizations of “inciting members of the community to keep protesting after the police has already reached understandings with them,” YNet reported.
The country’s premier, Benjamin Netanyahu, is set to meet the representatives of the Israeli Ethiopian community on Monday.



Police didn’t deploy officers of Ethiopian descent, fearing a conflict of interests that already led to clashes last week during a protest in Jerusalem, Haaretz reported.










More forces could be deployed if needed, security forces stressed.
This is the second such protest in a week: On Thursday, hundreds of demonstrators blocked streets and the Jerusalem Light Rail, and marched on the prime minister’s home.
Thirteen protesters and three policemen were injured in the clashes then, Times of Israel reported.
Over 135,000 Ethiopian Jews are Israeli residents, with most of them having immigrated in two waves, in 1984 and 1991.



Source: http://rt.com/news/255281-israel-protest-racism-violence/

Wednesday, April 29, 2015

በርካታ ወጣቶችን በጨለማ እየታፈሱ ነው


ሚያዝያ ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሊቢያና በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን አሰቃቂ አደጋ ተከትሎ ለተቃውሞ የወጡ ኢትዮጵያውያን በፌደራል ፖሊሶች ተደብድበው እንዲታሰሩ በተደረገ ማግስት፣ የኢህአዴግ የጸጥታ ሃይሎች በአዲስ አበባ በተለያዩ ክፍለከተሞች የሚገኙ ወጣቶችን በምሽት በማፈን ወደ እስር ቤት እያጋዙ ነው።
የከተማዋ ነዋሪዎች እንደተናገሩት ባለፉት ሶስት ቀናት ብቻ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጭ ተወስደው ታስረዋል መጪውን ምርጫ ተከትሎ ገዢው ፓርቲ ረብሻ ይነሳል በሚል ፍርሃት ወጣቶችን እያፈነ በማጋዝ ላይ መሆኑን ዘጋቢያችን ያነጋገራቸው ሰዎች ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በወንጅ ወረዳ የገዢው ፓርቲ ኳድሬዎች እናቶችን ብቻ በመሰብሰብ ልጆቻችሁን ምከሩ በማለት እያስፈራሩ መሆናቸው ተመልክቷል።
ባለፈው ረቡዕ በነበረው ተቃውሞ ላይ ተይዘው የተፈቱት ወጣቶች ለኢሳት እንደተናገሩት፣ በተያዙበት እለት ምግብና ውሃ ከመከልከላቸውም በላይ ይደበደቡ ነበር ። ወጣቶቹ ሲለቀቊ አሻራቸውን መስጠታቸውንና ከአሁን በሁዋላ በየትኛውም መንገድ ተቃውሞ ቢያደርጉ
የከፋ ጉዳት እንደሚደርስባቸው ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የአንድነት ፓርቲ አባል እና የሚሊየኖች ድምፅ አምደኛ የነበረው እስማኤል ዳውድ መታሰሩ ተዘግቧል።
ወላጅ እናቱ እንደተናገሩት ትላንት ከጠዋቱ ሁለት ሰአት ላይ ሲቪል የለበሱ ሰዎች ወደመኖሪያ ቤት መጥተው እስማኤልን ወስደው አስረውታል።
ሰዎቹ ሲወስዱት፦ ‹‹ፖሊስ ጣቢያ ቃል ሰጥተህ ትመለሰላህ›› ቢሉትም፤ አራዳ ፖሊስ ጣቢያ ቃሉን ከሰጠ በሁዋላ ግን እንደማይለቀቅ አስታውቀውት ወደ ወረዳ 9 ፖሊስ ጣቢያ መወሰዱን ወላጅ እናቱ ገልፀዋል።
በትላንትናው እለትም ከአራዳ ፖሊስ ጣቢያ ስልክ ተደውሎላቸው፤ ልጃቸው እስማኤል ችሎት መድሃኒያለም አካባቢ ወደሚገኘው ወረዳ 9 ፖሊስ ጣቢያ መዛወሩ እንደተገለፀላቸውም ተናግረዋል።
እስማኤል፣ ዛሬ ሚያዚያ 21 ቀን 2007 ዓመተ ምህረት ከረፋዱ 5፡30 ላይ ፒያሳ በሚገኘው አራዳ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን፤ በችሎቱ የተሰየሙት ሴት ዳኛ ‹‹በአራት ቀን ውስጥ ፖሊስ ምርመራውን አጠናቆ ለክስ የሚያበቃ በቂ ማስረጃ ካለው ፍርድቤት እንዲያቀርበው፤ አለበለዚያ ግን በነጻ እንዲያሰናብተው›› ትእዛዝ አስተላልፈዋል፡፡
ልጃቸው በምን ምክንያት እንደታሰረ ያውቁ እንደሆነ የተጠየቁት ወላጅ እናቱ ፦በረቡዕ ሰልፍ ላይ በመገኘቱ ምክንያት እንደሆነ በመጥቀስ፤ ከእሱም ሌላ ሁለት ጓደኞቹ ለእስር መዳረጋቸውን ገልፀዋል፡፡
ከስልፉ ጋር በተያያዘ ሰማያዊ ፓርቲ ስድስት አባሎቹ እንደታሰሩ ያስታወቀ ሲሆን፤ በ አቶ በላይ ፍቃዱ ይመራ ከነበረው ከቀድሞው አንድነት ፓርቲ ውስጥ ደግሞ ለእስር የተዳረጉት ቁጥራቸው ሶስት ደርሷል፡፡
እነሱም፦እስማኤል ዳውድ፣ ስንታየሁ ቸኮልና የፓርቲው የብሔራዊ ምክር ቤት አባል የነበሩት አቶ ዳዊት አስራደ ናቸው። በአገር ውስጥ ያለው ውጥረት እየጨመረ በመጣበት በአሁኑ ወቅት፣ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም በሊቢያ፣ ሳውድ አረቢያና የመን ዜጎች ላይ የደረሰውን ግፍ ማውገዛቸውን ቀጥለዋል።
በቤልጂየም ብራሰልስ ኢትዮጵያውያን ዛሬ በአውሮፓ ህብረት ጽ/ቤት ፊት ለፊት ተገኝተው ሀዘናቸውንና ቁጣቸውን ገልጸዋል። በቶሮንቶ አካባቢ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንም የሻማ ማብራትና የጸሎት ምሽትት በማድረግ ብዙ ሕዝብ በተገኘበት ከፍተኛ ሃዘናቸውን
ገልሰዋል፡፡ በስነስርአቱ ላይ የተለያዩ እምነት ተከታይ የሆኑ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን በተገኙበት በዚህ የሃዘን ቀን ኢትዮጵያውያን እጅ ለእጅ ተያይዘው በጋራ እንዲነሱ ጥያቄ ቀርቧል።
በኒዮርክም እንዲሁ የሻማ ማብራትና የጸሎት ስነስርአት ተካሂዷል።
Source:: Ethsat