Monday, June 29, 2015

ብአዴን እንደ ሞዴል የሞከራቸው ተቋማቱ በመክሰራቸው ሺዎች ለችግር ተጋለጡ


ሰኔ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ብአዴን እያስተዳደርኩት ነው በሚለው የአማራ ክልል የጀመራቸው የተለያዩ ተቋማት ውጤት አልባ በመሆናቸው ብዙዎቹ እየፈረሱና ዜጎችን ለችግር እያደረጉ መሆኑን ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ አመልክቷል።
የክልሉ ቴክኒክ እና ሙያ ኢንተርፕራይዝ እና የክልሉ ጥቃቅን እና አነሰተኛ ቢሮዎች በክልሉ የሚገኙ በሚልዮን የሚቆጠሩ ስራ አጦችን በተለያየ ሙያዎች በማሰልጠን የክልሉን የስራ አጥ ቁጥር ከመቀነስ ባሻገር ለልማት አስተዋጽዎ እያደረገ ነው ቢባልም በተግባር እየታየ ያለው የዚህ ተቃራኒ ነው። ተቋሙ በሚልዩኖች ለሚጠጉ ስራ አጥ ወጣቶቸ እና ስራ ፈላጊዎች የስራ እድል ፈጥሪያለሁ እያለ በየአመቱ ሪፖርት ያቀርባል። ይሁን እንጅ ከ93 በመቶ በላይ የሚሆኑት የተደራጁት የጥቃቅን እና አነስተኛ ወጣቶች ማህበራት ሙሉ በሙሉ መክሰማቸውን መረጃዎች አመልክተዋል።
ከሁሉም ክልሎች የአማራ ክልል ብቻ የጥቃቅንና አነስተኛ ስትራቴጂ መክሸፉን ለፌደራል መስሪያ ቤቱ ሪፖርት ያደረገ ሲሆን፣ ብዙ የተወራለትን ተቋም ከክስረት ለማዳን የአማራ ክልል ቴክኒክ እና ሙያ ኢንተርፕራይዝ እና የአማራ ክልል ጥቃቅን እና አነሰተኛ ቢሮዎችን በማዋሀድ ካለፉት 4 አመታት ጀምሮ ወጣቶችን ለማሰልጠን ሙከራ ተደርጓል። ይሁን እንጅ ከ4 አመታት ሙከራ በሁዋላ ተቋሙ ሙሉ በሙሉ መፍረሱ ታውቋል። ሁለቱን ተቋማት ለማዋሀድ በተሰራው የማዋቀር ስራ እስከ ገጠር ባሉ ወረዳዎች በነበረው አደረጃጀት 5 ሺ 300 ሰራተኞች ከስራ ውጭ ሆነው ለችግር ተጋልጠው ቆይተዋል።
በሽዎች የሚቆጠሩ ቤተሰቦች ከተበተኑ እና ይመጣል የተባለው የሚልዮኖች የስራ እድል ውጤታማ መሆን ባለመቻሉ እንዲሁም የክልሉ ምክር ቤት የበጀተው ከፍተኛ ገንዘብ ውጤት ሳያመጣ በማለቁ የፈረሱት ድርጅቶች ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ መወሰኑን መረጃዎች አመልክተዋል።
የክልሉ ንግድና ትራንስፖርት ባለስልጣን ፈርሶ የክልሉ ንግድ ቢሮ እና ትራንስፖርት ባላሰልጣን ቢሮ በሚል አዲስ አደረጃጀት እየተሰራ ሲሆን፣ 4ሺ 397 ሰዎች ከስራ ገበታ ውጭ ሁነዋል፡፡
በሌላ ዜና ደግሞ የማዳበሪያ አቅርቦት ከማህበራት ተቀምቶ ወደ አማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም እጅ መግባቱ በማህበራት ህልውና ላይ አደጋ የሚጋርጥ አሰራር መሆኑን የክልሉ አርሶአደሮች ተናግረዋል፡፡
በክልሉ ልዩ ልዩ ቦታዎች የሚኖሩ አርሶ አደሮች እንደገለጹት ከአሁን በፊት በህብረት ስራ ማህበራት አማካኝነት እየመጣ በግማሽ ክፍያና በዱቤ ለማህበሩ አባላት ሲከፋፈል የነበረው የማዳበሪያ አቅርቦት ሙሉ በሙሉ በገዢው መንግስት ስር በሚተዳደረው ንግድ ተቋም መዛወሩ ማህበራትን ፋይዳ በማሳጣት አርሶ አደሩ ግብአቱ በአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም በኩል እንዲከፋፈል የተደረገው ‘ ብድር አልከፈላችሁም ‘ በሚል ሰበብ የአርሶ አደሩን ሀብትና ንብረት በመቀማት ባዶ እጅ ለማድረግ እና በቁጥጥር ስር ለማስገባት ሆን ተብሎ በገዢው መንግስት ባለስልጣናት አቀነባባሪነት የተሰራ ደባ እንደሆነ ቅሬታ አቅራቢ አርሶ አደሮች ለዘጋቢያችን ተናግረዋል፡፡
የብድርና ቁጠባ ተቋሙ ከአሁን በፊት ለበሬ መግዣ በሚል ለአርሶ አደሩ በከፍተኛ ወለድ ያበደረውን ገንዘብ ለመመለስ መቸገራቸውን የሚገልጹት ቅሬታ አቅራቢዎች፣ አሁንም የማዳበሪያው ሽያጩን በዱቤ ለማቅረብ መሰናዳቱ በአንድ ጊዜ ሁለቱን ብድር ለመክፈል የማይችሉ አርሶ አደሮችን ሀብትና ንብረት በመውረስ ለልመና ብሎም ለስደት ለመዳረግ ሆን ተብሎ የሚሰራ በደል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አስተያየት ሰጭ አርሶ አደሮች ሲናገሩ የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ብድሩ እንዲከፈለው የሚጠይቀው ጥር ወር ላይ በመሆኑ ገበሬው ብድሩን ለመክፈል ምርቱን በብዛት ስለሚያወጣ እህሉ ይረክሳል፡፡ይህ መሆኑ ደግሞ ከአሁን በፊት ማህበራት ሲያደርጉት የነበረውን ጊዜ ጠብቆ በተሻለ ዋጋ በመሸጥ አርሶ አደሩ ተጠቃሚ የሚሆንበትን ሂደት የሚያሳጣቸው በመሆኑ ብድሩን በቀላሉ ለመመለስ እንደሚያስቸግራቸው ተናግረዋል፡፡
በአሁኑ ሰዓት አርሶ አደሩ እዳውን በመፍራት መሬቱ የሚፈልገውን የማደበሪያ ብዛት ሳይሆን አርሶአደሮች ባላቸው አቅም ብቻ እየዘሩ መሆኑን ይናገራሉ፡፡ሁለት ማዳበሪያ የሚፈልገውን መሬት በአንድ ማዳበሪያ ለመሸፈን የሚገደዱት እዳውን በመፍራት መሆኑን የሚናገሩት አርሶአደሮች ፣ ይህም በምርት ላይ ትልቅ አሉታዊ ተጽእኖ ሊፈጥር እንደሚችል አክለዋል፡፡ ብድሩን ለመስጠት በሚል ስበብ በየጊዜው ስብሰባ በመጥራት ስራ እያስፈቱት መሆኑን የሚናገሩት ቅሬታ አቅራቢዎች፣ ሁሉም አርሶ አደር ሂደቱን ሙሉ በሙሉ የማይቀበለውን ስራ እየሰሩ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
አርሶአደሮቹ የማዳበሪያ አቅርቦቱ ወደ ክልሉ ብድርና ቁጠባ የተዛወረበትን ምክንያት ሲጠይቁ፣ ‹‹ ማህበራት አቅማቸው እንዳይደክም በማሰብና ብድር የማይመልሱ አበላት በመኖራቸው ነው፡፡›› የሚል ምላሽ ከባለስልጣናት እንደተሰጣቸው አስታውሰው፣ የድሃ ድሃ ሆነው አቅም ያጠራቸው ጥቂት አርሶ አደሮች ካልሆኑ በስተቀር ሁሉም ብድሩን በጊዜው እንደመለሰ ይገልጻሉ፡፡
ብአዴን/ኢህአዴግ በአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋሙ አማካኝነት፣ አርሶ አደሩን ከሌሎች የገንዘብ ተቋማት በተለየ እጥፍ ወለድ በማስከፈል በቢሊዮን የሚቆጠር ሀብት ያከማቸ ሲሆን፣ ገዢው መንግስት አርሶ አደሩን በልዩ ልዩ ግብዓቶች አቅርቦት ሊረዳው ሲገባ የማህበራትን የስራ ድርሻ በመቀማት የፈላጭ ቆራጭነት አሰራሩን በስፋት መጀመሩ ምቾት እንዳልሰጣቸው ቅሬታ አቅራቢዎች ማናገራቸውን የክልሉ ዘጋቢ ገልጻለች።

መድረክ ምርጫውን በማስመልከት ቅድመ ሁኔታ አስቀመጠ


ሰኔ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስባ የሆነው መድረክ ባወጣው መግለጫ በ2007 ዓ ም በሀገራችን ተካሄደ የተባለው ምርጫ በሕግና ሥርዓት ያልተመራና በሕገ-መንግሥቱና በምርጫ ሕጎች የተደነገጉትን የነፃ፣ፍትሐዊና ታአማኒነት ያለው ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መርሖዎች በኃይል በተጣሱበት ሁኔታ የተፈጸመ በመሆኑ መድረክ የምርጫውን ሂደትም ሆነ ውጤት እንደማይቀበለው ገልጾ፣ ለዚህ አሁን ሀገራችን ለገባችበት አስቸጋሪ ሁኔታ መፍትሔ ለማስገኘት የተለያዩ እርምጃዎች እንዲወሰዱ በጥብቅ እጠይቃለሁ ብሎአል፡፡
በምርጫው ወቅት የታየውን ግዙፍ የሕግ ጥሰት አንድ ወገንተኛ ያልሆነ አካል ተቋቁሞ እንዲያጣራው፣ በ አራት የመድረክ አባሎች ላይ ግድያ በፈጸሙ ወንጀለኞች ላይ ተገቢው ክትትል ተደርጎ ለሕግ እንዲቀርቡና ፍትሐዊ ውሳኔ እንዲሰጥባቸው፣ ከምርጫው ቅስቀሳ ወቅት ጀምሮ በየምርጫ ክልሎቹ የታሰሩት አባሎቻችን ካለአንዳች ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈቱና የድብደባና የማሰቃየት ተግባራትን የፈጸሙባቸው የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች ለሕግ እንዲቀርቡ፣ ከምርጫው እንቅስቃሴ ወዲህ ቤታቸው የተቃጠለባቸው፣ የፈረሰባቸውና ንብረታቸው የተዘረፈባቸው አባሎቻቸው ሀብትና ንብረት በአስቸኳይ እንዲመለስላቸውና እንዲከፈላቸው፣ በንብረታቸው ላይ ጉዳት ያደረሱ ካድሬዎችና የጸጥታ ኃይሎች አባላትም በሕግ እንዲጠየቁ፣ በአሁኑ ወቅት በኢህአዴግ ካድሬዎች በማንአለብኝነት በሰላማዊ ዜጎች ላይ እየፈጸሙ የሚገኙት የማሸበር ተግባራት ማለትም በሰላማዊ ታጋዮቻችን ላይ በቀጣይነት እየተፈጸሙ ያሉት ግዲያዎች፣ ማስፈራራት፣ ወከባዎች፣ ዛቻዎችና የመሥራትና የመማር እንዲሁም እርዳታና አገልግሎት የማግኘት መብት በመንፈግ የሚፈጸሙ ሕገወጥ ተግባራት በአስቸኳይ እንዲቆሙ እንዲደረግና በዚህ አፍራሽና ፀረ ሰላም ተግባራቸው ምክንያት የሀገራችንና የሕዝባችን ሰላምና ደህንነት እንዳይናጋ ወቅታዊ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ መድረክ ጠይቋል።
እንዲሁም ይላል መድረክ በ2007 ዓ ም በሀገራችን የተካሄደው ምርጫ ከሀገራችን ሕገ-መንግሥትና የምርጫ ሕጎች ውጭ መንግሥታዊ ሥልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም ሕዝብን በማስፈራራት፣ በኃይልና በአፈና ገለልተኛ ታዛቢዎች በሌሉበት ገዥው ፓርቲ ራሱ ተወዳዳሪ፣ ዳኛና ታዛቢ ሆኖ ያካሄደውና በምንም መልኩ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ያልሆነና ታአማኒነት የሌለው ሕገወጥ ምርጫ
ስለሆነ፣ገዥው ፓርቲ በገለልተኛ የምርጫ አስተዳዳር አማካይነት ገለልተኛ ታዛቢዎች በተገኙበት ነፃ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ የሆነና ታአማኒነት ያለው ምርጫ ሊካሄድ በሚችልበት ሁኔታ ላይ ከመድረክና ሌሎች ሐቀኛ ሰላማዊ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር በአስቸኳይ በመደራደር ለነፃ፣ ፍትሐዊ፣ ዴሞክርሲያዊና ታዓማኒነት ላለው ምርጫ አመቺ ሁኔታ እንዲፈጠር ፣ በሀገራችን የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት እንዲረጋገጥ ሕጋዊ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ፣ እንደዚሁም ነፃ ፍትሐዊ ተዓማኒ ምርጫዎች ውስጥ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳይሳተፉ እንቅፋት የሆኑ ሕጋዊና ተቋማዊ ሁኔታዎችን ለማስወገድ ከኢህአዴግ ጋር ድርድር እንዲካሄድ ጠይቋል።
የሀገራችን ችግሮች እየተወሳሰቡና ከቁጥጥር ውጭ እየሆኑ ከሄዱ ኃላፊነቱ የኢህአዴግ ብቻ እንደሚሆን የሚገልጸው መድረክ፣ ኢህአዴግ የፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ምርጫን መንገድ ሙሉ በሙሉ በኃይል ቢዘጋም፣ በሕገመንግሥት የተረጋገጡትና ገና ጥቅም ላይ ያልዋሉ የሰላማዊ የትግል ፈርጆችን በመጠቀም አምባገነኑ የኢህአዴግ አገዛዝ ለሕግ የበላይነት እስኪገዛና ሰላማዊ የመፍትሔ ሐሳቦችን ተቀብሎ ሕገመንግሥታዊ መብቶች በተግባር እስኪረጋገጡ ድረስ የኢትዮጵያ ህዝብ ትግሉን እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።
መድረክ ያቀረበውን የትግል ጥሪ በዝርዝር እቅድ በማውጣት ተግባራዊ ለማድረግ ስለማቀዱ የገለጸው ነገር ለም።

የፕሮቪደንት ፈንዱ በገጠመው ከፍተኛ ተቃውሞ ለፓርላማ ሳይቀርብ በኮሚቴ እንዲሻሻል ተደረገ


ሰኔ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግል ሠራተኞች የፕሮቪደንት ፈንድ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ያለውን ገንዘብ ወደመንግስት በማስገባት ሠራተኞቹ በጡረታ እንዲታቀፉ በሚያስችል መልኩ የተደነገገው የግል ድርጅቶች የማህበራዊ ዋስትና አዋጅ ማሻሻያ በገጠመው ከባድ ተቃውሞ ምክንያት ለፓርላማው ሳይቀርብ በቋሚ ኮምቴዎች ውሳኔ እንዲሻሻል መደረጉን ዘጋቢያችን ገልጿል።
የማሻሻያ ሕጉ ከአንድ ወር በፊት ለፓርላማ ሲቀርብ አሁን በስራ ላይ ያለው ሕግ አንዳንድ ሠራተኞችን የፕሮቪደንት ፈንድ ተጠቃሚ ሲያደርግ አንዳንዶቹን ደግሞ በጡረታ ማቀፉ አድሎአዊ አሰራር አስከትሎአል፣ የመብትና የጥቅም ልዩነት ፈጥሮአል በሚል ከሰኔ 16 ቀን 2003 ዓ.ም በፊት ተቀጥረው ይሰሩበት በነበረበት የግል ድርጅት የፕሮቪደንት ፈንድ ያላቸው ሠራተኞች ገንዘባቸው ተወርሶ ወደጡረታ እንዲዛወሩ በረቂቅ አዋጁ መደንገጉ ከተሰማ ወዲህ በርካታ ሠራተኞች የራሳቸውን እርምጃ መውሰድ መጀመራቸው መንግስትን አደናግጦአል፡፡
አዋጁ ያጠራቀሙትንና ለአንድ የችግር ወቅት ይሆናል ብለው የሚያስቡትን ገንዘብ ያሳጣናል ብለው የሰጉ ሠራተኞች፣ ከአሰሪዎቻቸው ጋር በመመካከር የፕሮቪደንት ፈንድ ገንዘባቸውን አዋጁ ከመጽደቁ በፊት ያወጡ ሲሆን አንዳንድ የሰራተኞቹን ጥያቄ
ያልተቀበሉ አሰሪዎች ባሉባቸው መ/ቤቶች ሠራተኞች በጅምላ ስራቸውን በመልቀቅ የፕሮቪደንት ፈንዳቸውን እየወሰዱ መሆናቸውን መንግሰት በመረዳቱ ጉዳዩ የተመራለት የፓርላማው ቋሚ ኮምቴ አንቀጹ እንዲሻሻልና ሠራተኞች በፍላጎታቸው ብቻ በጡረታ እንዲታቀፉ በረቂቅ አዋጁ እንዲካተት አደርጎአል፡፡
አዋጁ ገና ለሕዝብና የባለሙያዎች አስተያየት እየተሰባሰበበት ሲሆን፣ ለፓርላማው ቀርቦ ሳይጸድቅ ባልተለመደ ሁኔታ አወዛጋቢው አንቀጽ መሻሻሉን በመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንዲነገር መደረጉ ከባድ የሕግ ጥሰት መሆኑን የገለጸው ዘጋቢያችን፣ የመንግሰት እርምጃ በሁኔታው መደናገጡን የሚያሳይ ነው ብሎአል።
የግል ድርጅቶች ማህበራዊ ዋስትናን በሚመለከት የቀረበውንና አሁን የሚሰራበትን አዋጅ ቁጥር 715/2003 ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ በሚኒስትሮች ም/ቤት ጸድቆ ለፓርላማ የቀረበ መሆኑም አይዘነጋም፡፡
የግል ድርጅቶች ማህበራዊ ዋስትና ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ ሕግ በግል ድርጅቶች ሠራተኞች ሰፊ ተቃውሞ እንዳጋጠመውና ሰራተኞችም ገንዘባቸውን እያወጡ መሆኑን በመጥቀስ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
በሌላ ዜና ደግሞ
የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የሚቀርቡለት አቤቱታዎች ፈጥኖ ውሳኔ መስጠት አለመቻል፣ የመልካም አስተዳደር እና የኪራይ ሰብሳቢነት ችግሮች አለመቀረፋቸውን ተከትሎ አገልግሎት ፈላጊዎችን በበቂ ሁኔታ ያለማስተናገድ ችግሮች ለገቢ አሰባሰቡ እንቅፋት መሆናቸውን ጠቅሶአል፡፡ በዚህም ምክንያት የንግዱ ማህበረሰብ በጣም ከሚማረርባቸው ተቋማት መካከል አንዱና ቀዳሚው የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን መሆኑ ተመልክቷል፡፡
የዋና ኦዲተር መ/ቤት በቅርቡ ለፓርላማው ባቀረበው ሪፖርት የአሰራር ዝርክርክነትና ለሙስና በር የሚከፍቱ አሰራሮች ከሚስተዋሉባቸው መንግስታዊ ተቋማት መካከል የገቢዎችና ጉምሩክ ባለለስልጣን አንዱ መሆኑን አመልክቷል፡፡
የገቢ ሰብሳቢ መ/ቤቶችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች በገቢ ቀረጥና ታክስ እንዲሁም በሌሎች ገቢ መሰብሰብን በሚፈቅዱ አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎች መሠረት የመንግስትን ገቢ የሰበሰቡ መሆኑን ለማረጋገጥ ኦዲት ሲደረግ በ25 መ/ቤቶችና በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ሥር ባሉ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በድምሩ ከ200 ሚሊየን ብር በላይ በገቢ ግብር፣ ቀረጥና ታክስ እንዲሁም በሌሎች ገቢ መሰብሰብ በሚፈቅዱ አዋጆች መሰረት ሳይሰበሰብ መቅረቱን አጋልጧል።

በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች የሚቀርቡት የፖለቲካ ክሶች ከጊዜ ወደ ጊዜ አስቂኝ እየሆነ ነው።


ሰኔ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከዚህ ቀደም በ1997 ምርጫ ወቅት በቅንጅት መሪዎች፣ በጋዜጠኞችና በሲቪክ ተቋማት መሪዎች ላይ የቀረበው ክስ ፣ 24 ሰአታት አስቂኝ ፊልም የሚል ስያሜ ተሰጥቶት ነበር። በፍርድ ቤቱ የነበረውን ሁኔታ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና የቃሊቲው መንግስት በሚል ርእስ ዘርዝሮ ማቅረቡ ይታወቃል።
በቅርቡ አይ ኤስ ኤስ የተባለው አሸባሪ ድርጅት በ30 ኢትዮጵያውያን ላይ የወሰደውን ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ ለማውገዝ መንግስት በጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ተፈጥሮ የነበረውን ተቃውሞ መርተዋል፣ በተቃውሞው ተሳትፈዋል እየተባሉ በእስር በሚሰቃዩ ወጣቶች ላይ የሚደርሰው ክስም እንዲሁ ፈገግ እያሰኘ ነገር ግን በዚያው ልክ እያሳዘነና አገራችን የገባችበትን የወርደት ደረጃ እያመላከተን ነው።
ቴዎድሮስ አስፋው ፣ ያሬድ ደመቀና አንዋር ከድር በተባሉ ወጣቶች ላይ የቀረበው ክስ እንዲህ ይላል ” ተከሳሽ የሃሰት ወሬዎችን በማውራት ጥላቻና የፖለቲካ ሁከት ለመቀስቀስ በማሰብ በ14/08/07 ዓም ከጧቱ 12 ሰአት ሲሆን በአዲስ አበባ ክ ከተማ በ01/02/03 በአሸባሪዎች ጥቃት ምክንያት ተጠርቶ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ሰዎችን በመሰብሰብ ” መለስ የሞተው ደንግጦ ነው፣ ሃይለማርያም ደሳለኝ በቁሙ የሞተ ነው” የሚል ሃሰተኛ ወሬዎችን በማውራት ሁከት መቀስቀስ ወንጀል ተከሷል። ”

Time to Expose the Brutal Regime in Ethiopia


The US leadership through a wrong foreign policy is denying the over 90 million Ethiopian peoples for sake of a disguise “national interest of the USA”. It is supporting one of the most brutal regimes in the world. It is using tax payer’s money to fund the tyrant regime that stayed on power since 1991 by dominating all political parties illegally and with force and corruption. Democracy is nominally used while the journalists are jailed, killed or are forced to exile. It divided the people ethnically and putting them in constant conflict while exploiting them, evicting the people from their historical lands and birth places while selling land to foreign scavengers with low price for its benefits. While regime in Ethiopia is corrupt, brutal and dictatorial, it brands itself as fighter of terrorism while it leads a state of terror over Ethiopians.

On the other hand the Obama regime denied the Ethiopian people while supporting dictatorship and brutality. Obama actually stood against human rights in Ethiopia. Hence it time to expose the brutal regime so that the leading nation can revise its foreign policy. This can happen if all opposition forces and advocates of democracy and human rights stand together for their common cause. This is the time to show that we have a common enemy. Please stand together and expose the regime at this critical time in history.

Time to expose the Brutal Regime in Ethiopia


Source:http://michaelab384

Ignoring Abuse in Ethiopia: DFID and USAID in the Lower Omo Valley







Southern Ethiopia’s Lower Omo Valley is one of the most culturally and biologically diverse areas in the world, yet the Ethiopian government is transforming more than 375,000 hectares (1450 sq. miles) of the region into industrial-scale plantations for sugar and other monocrops. A vast resettlement scheme for the local ethnic groups is accompanying these plans, as 260,000 local people from 17 ethnic groups who live in the Lower Omo and around Lake Turkana—whose waters will be taken for plantation irrigation—are being evicted from their farmland and restricted from using the natural resources they have been relying on for their livelihoods.
                
The plantations are being installed and ethnic and pastoral communities are being forcibly resettled with the help of the Ethiopian military, which has become a central player in the implementation of the Ethiopian government’s development plans. Forced evictions, denial of access to subsistence land, beatings, killings, rapes, imprisonment, intimidation, political coercion, and the denial of government assistance are all being used as tools of forced resettlement. Meanwhile, international donors have been accused of supporting the programs connected with the resettlement sites.
          
               In response to these criticisms, a group from the United States Agency for International Development (USAID) and the UK’s Department for International Development (DFID) conducted a joint field investigation in the Lower Omo in January 2012. Although this group heard many credible accounts of abuses connected to the resettlement or “villagisation” program, the official stance of the United Kingdom government has since been to repeatedly insist that the “the Department for International Development was not able to substantiate the allegations of human rights violation it received during its visit to South Omo in January 2012.” Similarly, the US State Department’s Ethiopia 2012 Human Rights Report released in April 2013 indicates that donors’ visits “did not find evidence to support this claim [of human right violations] during visits.” DFID and USAID also reported this unsubstantiation of allegations of human rights abuses to the Development Assistance Group (DAG), which is made up of 26 of the major aid agencies that donate to Ethiopia including the UNDP, IMF, and the World Bank.
                 
             This report provides unique insight into the investigation conducted by the donor agencies in January 2012. In stark contrast with the official discourse, testimony from the affected communities shows that egregious human rights violations have taken place. The author accompanied the assessment team as its translator and has audio recordings of the interviews conducted in several Lower Omo communities. Transcripts of these recordings, made public with this report, leave no room for doubt that the donor agencies were given highly credible first-hand accounts of serious human rights violations during their field investigation and they have chosen to steadfastly ignore these accounts.   


Download full report here : brief ignoring abuse ethiopia

Sunday, June 28, 2015

ሚኒስትር ዲኤታዎች ድምጽ አልባና ደካሞች ናቸው ተባሉ


ሰኔ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-“በኢትዮጵያ ያሉ ሚንስትር ድኤታዎች ድምፅ አልባ እና ተሳትፎ የሌላቸው ደካማዎች ናቸው” ሲል የኢህአዴግ ጽ/ቤት የአመራር ግንባታ የመለስ ዜናዊ የአመራር ግንባታ ክፍል ያወጣው ደብዳቤ አመለከተ። ደብዳቤው ዝቅተኛ እና መካከለኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ ያላቸውን ሚኒስትር ድኤታዎች ዘርዝሮ አስቀምጧል።
በአቶ አዲሱ ለገሰ የሚመራው እና ከፍተኛ የኢህአዴግ አባላትን ብቻ የሚያሰለጥነው የኢህአዴግ አመራር ማሰልጠኛ ክፍል የአመራሮችን አቅም በመገምገም በሚንስትር ድኤታ ደረጃ ያሉትን ብቻ ለይቶ በመጥራት ውይይት አካሂዷል፡፡ በዚህም በመሪነት ደረጃ ለኢህአዴግ አቅም መጎልበት አስተዋጽኦ ያላደረጉ እና ቀዳሚ መሆን ያልቻሉ ያላቸውን አካላትን ዘርዝሮ አስቀምጧል፡
በዝቅተኛ ደረጃ የተመደቡት የፊደራል ጉዳዩች ሚንስቴር ሚንስተር ድኤታ አቶ ሙሉጌታ ውለታው፣ የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር ድኤታ አቶ ወንዲራድ ማንደፍሮ፣ የኢፌድሪ የውጪ ጉዳይ ሚንስትር ድኤታ አምባሳደር ብርሀነ ገብረክርስቶስ፣ የትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ድኤታው አቶ ፉኢድ ኢብራሒም፣ የኢንዱስትሪ ሚንስትር ድኤታ ልዩ አማካሪ አህመድ ኑሩ፣ የባህልና ቱሪዝም ሚንስትር ድኤታ አቶ ሙልጌታ ሰኢድ ፣ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚንስትር ድኤታ አቶ ሽመልስ ከማል፣ የትምህርት ሚኒስትር ሚንስትር ድኤታ ዶክተር ካባ ኡርጌሳ፣ እንዲሁም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚንስትር ድኤታ አቶ ማህሙድ አህመድ ጋአስ ናቸው።
በመካከለኛ ደረጃ የተቀመጡት ደግሞ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ታደሰ ኃይሌ፣ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚንስትር ድኤታ አቶ ጌታቸው ነጋሽ፣ የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ድኤታ አቶ አህመድ ሽዴ እና የፍትህ ሚኒስትር ድኤታ አቶ ብርሃኑ ጸጋዬ ናቸው።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ በቃሉ ዘለቀ ባለባቸው የአቅም ውስንነት ምክንያት ወደ ሚንስትርነት ማእረግ ደረጃ ማደግ ስለማይችሉ የአቅም ግንባታ ስልጠና በክረሙቱ ተከታታይ ወራት ያስፈልጋቸዋል ተብሎአል። ይህም ሁኖ መሻሻል ካላሳዩ ከስልጣናቸው ወርደው በምትካቸው በአዲሱ ሰው እንዲተኩ የኢህአዴግ አመራር ማሰልጠኛ ኢንስትትዩት በአሁኑ ስያሜው የመለስ አመራር ማሰልጠኛ አካዳሚ ሃላፊ የሆኑት አቶ አዲሱ ለገሰ አስተያየታቻውን አስፍረዋል፡፡
የከፍተኛ አመራሩ ምደባ ግምገማ ኮሚቴ ተዋቅሮ በድክመት ፣ ጥንካሬ እና አማራጭ ተብሎ እየተለየ ሲሆን ፣ ከነድክመታቸው የሚያሰቀጥላቸውንና ወደ አመራር የሚያመጣቸውን አዳዲስ የፖለቲካ መሪዎች ስም ዝርዝር እና ግለ ታሪክ ተዘጋጅቶ እንዳለቀና እንደደረሰን ለማቅረብ እንሞክራለን፡፡