Thursday, September 3, 2015

ኮንቴይነር በተገኘ ቁጥር ‹‹ኢትዮጵያዊ ተደብቋል› ›መባል ተጀምሯል – የ10 ዓመት ታዳጊ ይገኝበታል


ከዳዊት ሰለሞን

በዛምቢያ ሴሬንጄ በተሰኘች ግዛት ፖሊስ 100 ኢትዮጵያዊያንን በመኪና ተጭነው ሲያመሩ መያዙን የአገሪቱ ዴይሊ ሜይል ጋዜጣ አስነብቧል፡፡
ስደተኞቹ ከናኮንዴ ሳይነሱ እንዳልቀሩ የጠቀሰው ፖሊስ ካኖና በተባለ የፍተሻ ኬላ በመኪናው ላይ በተደረገ ፍተሻ ሰዎቹ ተደብቀው መገኘታቸውን ጠቅሷል፡፡መኪናው በጫነው ኮንቴይነር በዛምቢያ ተወዳጅ የሆነውን ካፔንታ (የደረቀ አሳ) ሲያመላልስ የነበረ መሆኑን ጋዜጣው አውስቷል፡፡
ፖሊስ በናኮንዴ ድንበር አቋርጠው ኢትዮጵያዊያኑ ያለ ህጋዊ ፈቃድ በመግባታቸውና እነርሱን ለማዘዋወር ክፍያ የተፈጸመላቸውን ዛምቢያዊያንን እንደሚከስም ፖሊስ ነገረኝ ያለው ጋዜጣው ዘግቧል፡፡

ሎምቤ ካሙኮሺ ኮሚሽነር ናቸው ለጋዜጣው ‹‹100 ህገ ወጥ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞችን ያሳፈረ መኪና መያዛችንን አረጋግጥላችኋለሁ፡፡ከእኛ ጋር በመስራት ላይ የሚገኘው የስደተኞች መስሪያ ቤታችን ስደተኞቹን የኢቦላ ምርመራ ያደረገላቸው ሲሆን ሌሎች ምርመራዎችንም እያደረገ ይገኛል››ብለዋል፡፡

ኮሚሽነሩ ህገ ወጥ ያሏቸውን ስደተኞች ያዘዋወሩ ያሏቸውን ሶስት የአገራቸውን ዜጎችን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውንም አስረድተዋል፡፡ኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች ከ10 -50 የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን የተናገሩት ኮሚሽነሩ የሚበዙት ወጣቶች ናቸው ማለታቸውን ጋዜጣው አስፍሯል፡፡
100ዎቹ ስደተኞች በአሁኑ ወቅት በዛምቢያ ሙኮቤኮ በተባለ ወህኒ ቤት ይገኛሉ ተብሏል፡፡በቅርቡ በሞያሌ ድንበር በማቋረጥ ወደ ኬንያ የገቡ 100 ስደተኛ ኢትዮጵያዊያንን የአገሪቱ ፖሊስ ማስታወቁ አይዘነጋም፡፡ስደተኞቹ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማምራት የተንቀሳቀሱ መሆናቸውም ይነገራል፡፡ከኬንያ እስከ ደቡብ አፍሪካ መዳረሻ ያሉ አገራት ኮንቴይነሮችን የጫኑ መኪኖችን በድንበር አካባቢ ሲያገኙ‹‹ኢትዮጵያዊያን ይኖራሉ››በማለት ጠንከር ያለ ፍተሻ ማድረግ መጀመራቸውን በሂደቱ የተሳተፉ ሰዎች ሲናገሩ ይደመጣል፡፡

Source:: Zehabesha

Wednesday, September 2, 2015

በደቡብ ኦሞ የሰፈሩ የሰራዊት አባላት መጥፋታቸውን ተከትሎ ነዋሪዎች እየታሰሩ ነው


ነኅሴ ፳፯ (ሀያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ኦሞ ዞን በሃመር ወረዳ በሃመር ብሄረሰብና በዞኑ ፖሊስ መካከል ተፈጥሮ የነበረውን ግጭት ተከትሎ በአካባቢው የሰፈረው የአንድ ሻለቃ ጦር አባላት በርካቶቹ ኮብልለው በመጥፋታቸው ፣ ለወታደሮቹ መጥፋት ምክንያት ናቸው የተባሉ ሰዎች ተይዘው ታስረዋል። በመከላከያ ሰራዊቱ አባላት መካካል የሚታየው አለመተማማንና ልዩነት በመስፋቱ እርስ በርስ እስከመጋጨት ደርሰዋል።
ከወር በፊት በሃመር ወረዳ በተፈጠረው ግጭት በርካታ የወረዳው ነዋሪዎችና ፖሊስ አባላት ተገድለዋል። ግጭቱን ለማብረድ አንድ ሻለቃ ጦር በተለያዩ አካባቢዎች እንዲሰፍር ተደርጓል። ይሁን እንጅ በወታደሮቹ መካካል መተማመን በመጥፋቱ ከመካከላቸው በርካታ ወታደሮች በመኮብለላቸውና የደረሱበት ባለመታወቁ፣ አመራሮቹ ወታደሮች እንዲጠፉ አድርገዋል ያሉዋቸውን የሞተር አሽከርካሪዎች ይዘው አስረዋል። በቁጥጥር ስር ከዋሉት አሽከርካሪዎች መካከል ጌታ ጫን ያለው ወርቁ፣ አሚኑ ትኩና አሚኑ ሃሰን ይገኙበታል። አሽከርካሪዎቹ ፍርድ ቤት ቀርበው፣ ከ15 ቀናት የእስር ጊዜ በሁዋላ በዋስ ሲፈቱ፣ ወታደሮቹን በማሸሹ ሂደት ተሳትፈዋል የተባሉ በርካታ ወታደሮች በአርካሻ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው ይገኛሉ።
በመጀመሪያው ዙር ከጠፉት የሰራዊት አባላት መካከል 7ቱ የከባድ መሳሪያ አስተኳሾች ናቸው።
አንዳንድ የሰራዊቱ አባላት ደግሞ በአካባቢው ህዝብ ላይ እየፈጸሙት ያለው ወንጀል በዲመካና ቱርሚ የሚኖሩ ነዋሪዎችን አስቆጥቷል። ወታደሮቹ ህጻናትንና ባለትዳር ሴቶችን ሳይቀር አስገድደው በመድፈር በጤናቸውና በትዳራቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ ነው። የወታደሮቹን ጥቃት በመፍራት የአካባቢው ሴቶች ወደ ጂንካ ከተማ እየኮበለሉ ነው።
እስካሁን ድረስ ጉዳት ከደረሰባቸው ሰዎች መካከል የአቶ አረጋ ባለቤት፣ ለቤተሰባቸውና ለግለሰቦች ደህንነት ሲባል ሙሉ ስማቸውን የማንጠቅሳቸው ባለቤታቸው፣ እና የ11 አመት ህጻን ልጃቸው በወታደሮች ተደፍረዋል። አቶ ቢረጋ በባለቤታቸውና በልጃቸው ላይ ግፉን የፈጸሙትን ወታደሮች ለፍርድ ለማቅረብ ቢንቀሳቀሱም፣ በመርማሪ ፖሊስ ዮሴፍ ክፉኛ ተደብድበው ፣ እንዳይንቀሳቀሱ ተደርጓል።
እንዲሁም የአቶ ገልለሎ ልጅ የሆነችው የ8 አመቷ ህጻን ልጅ፣ በወታደር ከተደፈረች በሁዋላ ራሱዋን ስታ ፣ በዲመካ ጤና ጣቢያ ህክምና ተደርጎላት ከሞት ተርፋለች።
ከደቡብ ኦሞ ዞን ዜና ሳንወጣ ፣ በቅርቡ በዞኑ በደረሰው የመብራት ትራንስፎርመር ፍንዳታ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ተለይተው ታውቀዋል።
በበና ጸማይ ወረዳ በቃቆ ቀበሌ ነሃሴ 21 ፣ 2007 ዓም በደረሰው ፍንዳታ ፣ በቆቃ ጤና ጣቢያ ላብራቶሪ ሙያተኛ የነበረች ወ/ት ምሳ ታሪኩ አያሌው ወዲያውኑ ህይወቷ ሲያልፍ፣ ወ/ሮ መሰለች ቶጣሮ፣ ወ/ሮ ህይወት አበጀ፣ ወ/ሮ አዲስ አለም ውሉቃ፣ መ/ርት ጥሩየ አድማሴ፣ ወጣት ዘካሪያስ ዮሴፍ፣ አቶ በየነ ክብሪትና አቶ ደጀኔ ተፈሪ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው አሁንም በህክምና ላይ ሲገኙ፣ ሌሎች 13 ሰዎች ደግሞ ታክመው ወደ ቤታቸው ተመልሰዋል።
በእለቱ ከቀኑ ሰባት ሰዓት ላይ በቃቆ 1፤በቀያፈር 3፤በዲመካ 1፤በጂንካ 2፤በሜጸር 1፤በድምሩ 8 ትራንስፎርመሮች የፈነዱ ሲሆን፣ በቃቆዉ ፍንዳታ የዋናዉ መስመር ሽቦ በመበጠሱ በአካባቢዉ በሚገኘዉ ምግብ ቤት ላይ ወድቆ በሰው ህይወትና ንብረት ላይ

ቤቱ ለሶስተኛ ጊዜ የፈረሰበት ወጣት ራሱን አጠፋ


ነኅሴ ፳፯ (ሀያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ ፣ ታምራት ታንቱ ባጫ የተባለ ወጣት፣ ቤቱ ለሶስተኛ ጊዜ በመንግስት አፍራሽ ግብረሃይሎች መፍረሱን ተከትሎ፣ ራሱን ያጠፋ ሲሆን፣ ባለቤቱም ራሱዋን ስታ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ውስጥ ጸሎት እየተደረገላት ነው። ወጣት ታምራት ትናንት ነሃሴ 26 የቀብሩ ስነስርአት ተፈጽሟል። ሚሚ ባቴ የተባለች የአንድ ሳምንት መጫትም በላዩዋ ላይ ቤቷ በመፍረሱ፣ ጎዳና ላይ ወድቃለች። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የታሰሩ ወጣቶችም አሉ። እስካሁን ድረስ በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤቶች መፍረሳቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። በዚሁ ከተማ ትናንት ምሽት በንግድ ቤቶች ላይ በተነሳ ቃጠሎ ከ100 በላይ የንግድ ድርጅቶች ወድመዋ

በግለሰቦች እጅ የሚገኘውን የነፍስ ወከፍ መሳሪያ መልሶ ለመቀማት እንቅስቃሴ ተጀመረ፡፡


ነኅሴ ፳፯ (ሀያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአማራ ክልል ከምርጫ 2007 በፊት ህብረተሰቡ መሳሪያ እንዲታጠቅ በመፍቀድ ህጋዊ ያደረገውን የመሳሪያ ፈቃድ በመንጠቅ መሳሪያዎችን ለመሰብሰብ ስልቶችን እየቀየሰ መሆኑ ምንጮች ለኢሳት አስታውቀዋል፡፡
የክልሉ ሚሊሺያ ጽህፈት ቤት ህገወጥ የጦር መሳሪያ ህጋዊ ለማድረግ ምዝገባ ካካሄደ በኋላ የመሳሪያ ፍቃድ በመስጠት ህብረተሰቡ ራሱን እንዲከላከልበት መፍቀዱን ተከትሎ፣ ከአጎራባች ክልሎች በተለይም ከትግራይ ክልል በተሰማው ተቃውሞ በየግለሰቡ እጅ ያለውን ነፍስ ወከፍ መሳሪያ ለመሰብሰብ እንቅስቃሴ መጀመሩን ከስፍራው የደረሰን ዜና ያመለክታል፡፡
ሰሞኑን ግልጽ ባልሆነና አብዛኛው የህብረተሰቡ ክፍል ሊያየው በማይችል ሁኔታ አጫጭር ማስታወቂያዎችን በክፍለ ከተማ ደረጃ በማውጣት ከአሁን በፊት ጊዜያዊ የመሳሪያ ፈቃድ የወሰዱ ሁሉ በየሚኖሩበት አካባቢ በመገኘት ለህዝብ እንዲያስተቹና የህዝቡን ይሁንታ ካገኙ ቋሚ ፈቃድ ለመስጠት በተጠቀሰው ጊዜ የማይገኝ መሳሪያውን ገቢ ለማድረግ የሚያስችለውን አካሄድ መጀመሩ ታወቋል፡፡
የስብሰባው ጥሪ ማስታወቂያ የታጠቁ አካላት በህዝብ ይተቻሉ ቢልም በተጠቀሰው ቀን ህብረተሰቡ ተገኝቶ እንዲተቸ የተደረገ ጥሪ አለመኖሩ በገዢው መንግስት የታሰበ ተንኮል እንዳለ ጠቋሚ መሆኑን ምንጮች ይናገራሉ፡፡
ከአሁን በፊት ህጋዊ ሆነዋል በማለት ከእያንዳንዱ ባለመሳሪያ ከሁለት መቶ ሃምሳ ብር በላይ በመሰብሰብ መታወቂያ መስጠቱ እየታወቀ በአጭር ጊዜ ቀርባችሁ በህዝብ ካልተተቻችሁ መሳሪያውን እንነጥቃለን የሚል መንፈስ ባለው ማስታወቂያ ግልጽ ባልሆነ ሁኔታ መጠራታቸው አግባብ አንዳልሆነ ታጣቂዎች ይናገራሉ።
የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ሚሊሺያ ጽህፈት ቤት በልዩ ልዩ ክፍለ ከተሞች ምዝገባውን ለማካሄድ ባሳለፍነው ሳምንት መጨረሻ ሙከራ ቢያደርግም ምንም አይነት ታጣቂ ቀርቦ አለማስመዝገቡን ለማወቅ ተችሏል፡፡
‹‹ የመሳሪያ ፈቃዱ በየአካባቢው አመራሮች በወቅቱ ተተችቶ እንድንይዝ ተፈቅዶልናል፡፡ ›› የሚሉት መሳሪያ ታጣቂዎች ፣ ‹‹ በወቅቱ በአመራሮች ስንገመገም መያዝ አይፈቀድላችሁም ብንባል ለመሳሪያ ግዢ ያወጣነውን ከሐምሳ ሽህ ብር በላይ አንከስርም ነበር፡፡ ›› በማለት አሁን የገዢው መንግስት ሊሰራ ያሰበው ሴራ ደም መፋሰስን ሊያስከትል እንደሚችል ይናገራሉ፡፡
በአብዛኛው የሰሜን ጎንደር የሚገኙ ታጣቂዎች ለአንድ ክላሽንኮቭ መሳሪያ እስከ ስልሳ ሽህ ብር በማውጣት ገዝተው ለራሳቸውና ለንብረታቸው መጠበቂያ ቢያስፈቅዱም፣ አሁን በተጀመረው መሳሪያዎቹን የመንጠቅ እንቅስቃሴ በመቃወም ትጥቅ አንፈታም በማለት ከገዢው መንግስት አመራሮች ጋር መፋጠጣቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡
በኢህአዴግ ግምገማ ወቅት የህወሃት ጻሃፊ፣ የክልሉ መሪ ገዱ አንዳርጋቸው፣ አማራውን እያስታጠቀ፣ ራሱን ጄኔራል አድርጎ ሾሟል በማለት መገምገማቸውን ኢሳት መዘገቡ ይታወሳል። ሁለቱ ክልሎች በአጎራባች ወረዳዎች የይገባኛል ጥያቄ እየተወዛገቡ ነው። የትግራይ ክልል አማራ ክልል ህጋዊ የጦር መሳሪያ ፈቃድ መስጠቱን አጥብቆ ተቃውሞ ነበር። አሁን በህዝብ ግምገማ ስም መሳሪያ ለመቀማት የተላለፈው መመሪያም ከዚሁ ተቃውሞ ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል ምንጮች አስተያየታቸውን አስፍረዋል።

አዲስ አበባ መስተዳድር ከ 4 ሺ በላይ ሰራተኞችን ተጠያቂ ሊያደርግ ነው


ነኅሴ ፳፯ (ሀያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መስተዳድሩ 221 አመራሮችንና 4 ሺ 100 ሰራተኞችን ገምግሞ ጥፋተኛ ብሎአቸዋል። ሰራተኞቹ በህግ ይጠየቃሉ ተብሎአል።
ኢሳት የሰራተኞችን ግምገማ በተመለከተ ከወር በፊት ባቀረበው ዘገባ፣ አብዛኞቹ ሰራተኞች እና አመራሮች ዝቅተኛ ነጥብ እንደተሰጣቸውና ሊባረሩ እንደሚችሉ ገልጾ ነበር።
በዚሁ ግምገማ ምክትል ከንቲባው አቶ አባተ ስጦታውም ዝቅተኛ የግምገማ ነጥብ የተሰጣቸው በመሆኑ፣ ከሚቀነሱት መካካል ሊሆኑ ይችላሉ።

Oromo or Somali? Sometimes St. Cloud isn’t sure

On many occasions in St. Cloud, Dotoo Nebi noticed that something about his slim body, average height and dark complexion sorts him into a community he technically doesn’t belong to: Somalis.
“People here think I’m Somali,” Nebi said, seeming bewildered. “We’re not Somalis. We have a different language. We’re from a different part of the world.”
Indeed, they’re from a different country. Nebi, for example, hails from the Agarfa village of Ethiopia, an East African country of more than 94 million people.
Twenty-six years ago, Nebi was born into the country’s largest ethnic group, Oromo, which has spent decades fighting against the Ethiopian authoritarian regime for recognition and independence.
That struggle still continues in the region, giving birth to a seething unrest that has uprooted many families, including hundreds who made St. Cloud their home.
“They took all of our cows, goats and horses,” Nebi said of the Ethiopian soldiers, who roamed in his village. “Every single day, we used to see (them). We were scared for our lives.”
That fear finally brought Nebi to St. Cloud, where he now serves as the executive director of the Midwest Oromo Community, a nonprofit organization that provides service to his Oromo community in Central Minnesota.
The soft-spoken leader is at times surprised that many people here don’t differentiate his community from the Somalis.
On a recent day in the St. Cloud Wal-Mart, he said, an American woman had a heated argument with a Somali woman. When the quarrel cooled off, he said, the same American woman approached him, stared at him and yelled out, “I hate Somalis.”
“She thought that I was a Somali,” he said. “I didn’t say anything.”
Story continues below.
Geshe Hassen, another member of the St. Cloud Oromo community, said he had a similar experience. Many times, he said, people are genuinely confused — they just don’t know much about the Oromo community and its history.
“It doesn’t bother me,” Hassen said. “But I just wish people would know that we’re from Ethiopia.”
Members of the broader community aren’t the only people who misidentify the Oromo group. Hussein Mohamud, who is a Somali, said he speaks in Somali with Oromo people when he sees them on the streets.
“The way we dress and our physical appearance are the same,” he said. “Even our people can’t sometimes tell the difference between the two communities.”
Childhood years in Ethiopia
Nebi’s story is different from that of Somalis — and it’s remarkable in its own way. He came of age at a time when writing in his native Afaan Oromo language was a crime in Ethiopia.
The language had remained nothing more than an oral tradition until in the early ’70s, when leaders of the Oromo Liberation Front made Afaan Oromo the official language in the areas they controlled.
In response, the former Ethiopian dictator Lt. Col. Mengistu Haile Mariam banned the language in the country.
Nebi, however, secretly learned to write and read it from his father, Kedir, who had also taught scores of others in the Oromo community.
When Mengistu’s government collapsed in 1991, Nebi’s father joined the liberation movement for the betterment of the Oromo people — risking persecution.
About a decade later, life in the region became too dangerous for Kedir; he moved to the United States in 2001.
Nebi, on the other hand, moved to Kenya with his family of eight in 2004.
Two years later, Nebi, who completed his middle and elementary school education in Ethiopia, came to Minnesota in 2006. “When I came here, I didn’t know English,” he said, adding that when he sat for the exam for placement at Arlington Senior High School in St. Paul, he wrote the exam in his native language.
His math and science skills, though, were above average. When he began to study biomedical science at St. Cloud State University in 2008, he worked as a math and science tutor at the university’s campus.
Oromo community service
Through the Midwest Oromo Community, Nebi said he hopes to educate St. Cloud residents about his Oromo people — a community that has both Muslims and Christians, whose language and country is different than Somalis and their homeland.
According to Nebi’s estimation, St. Cloud is home to more than 500 Oromo people who started arriving in 2008. Many of them struggle with language and cultural barriers as well as education and transportation issues, Nebi noted.
Some members of the community applauded Nebi for his service.
Hassen, who is also Nebi’s longtime friend, remembers Nebi as an effective organizer even when the two were in college. “He used to organize us in college,” he said of Nebi. “Because of him, we became more involved in campus activities.”
He added: “Now he’s organizing the community the same way he used to organize college students. I really like his leadership style.”
Since Nebi became the head of the Midwest Oromo Community in 2013, he’s created several educational programs and services to empower his community. They are aimed at older people, women and youth in the Oromo community.
“We provide many programs,” said Nebi, who’s also a paraprofessional at North Junior High School, “like community health education, and mental illness and immigration services.”

22 Years for Torturer OK With 10th Circuit

By EMMA GANNON

DENVER (CN) - Twenty-two years in prison is a fine sentence for an Ethiopian torturer who stole another man's identity and fled to the United States to duck prosecution, the 10th Circuit ruled Tuesday.
     Kefelegne Alemu Worku used the name Habteab Berhe Temanu to hide in Denver until 2012, when immigration agents found him after several witnesses identified him as a member of the Ethiopian Red Terror campaign of the 1970s. He was accused of torturing and killing dozens of political prisoners while working as a prison guard, and stealing the identity of an Ethiopian man.
     "Four of the victims testified that they had been tortured by Mr. Worku," 10th Circuit Judge Robert Bacharach wrote for the unanimous three-judge panel.
     A Denver federal judge Worku the maximum sentence on each of count: unlawful procurement of citizenship, visa fraud, and identity theft.
     Worku appealed, claiming he'd been subjected to double jeopardy, that he had permission to use Temanu's identity, that there was no proof he came to America to dodge prosecution for human rights violations, and that the witnesses who identified him as a sadistic prison guard had been subjected to "improperly suggestive photo arrays." He also claimed his sentence was "substantively unreasonable."
     The 10th Circuit rejected all of his challenges.
     Though Worku claimed the third count of identity theft was the same as the first count, unlawful procurement of citizenship, the crimes are not "based on the same conduct," Bacharach wrote.
     Nor was the judge persuaded by Worku's claim that he had "lawful authority" to use Habteab Berhe's identity, because he had permission from the man's children.
     "Mr. Worku has not presented any cases suggesting that the children could lawfully allow another person to use their father's identity," Bacharach wrote. "Mr. Worku does not allege consent from the person whose identity was used: Mr. Berhe."
     Bacharach cited the U.S. District Court ruling that Worku "had persecuted others 'because of race, religion, national origin, membership in a particular social group, or political opinion,'" and lied about it. He also was accused of having paid a broker to help with the identity theft.
     "Together, these facts create a plausible inference that Mr. Worku wanted to come to the United States to avoid punishment for his human rights violations in Ethiopia," Bacharach ruled.
     Nor was the court persuaded by Worku's claim that "the photo arrays were unduly suggestive, resulting in a deprivation of due process." Worku claims that of the four photo arrays used, his photo was "the brightest and clearest" in the first two. In the third, Worku said, his photo was the most "heavily shadowed." He was the only man shown wearing a "large hooded winter jacket," only one man had hair on his head, and two of the men didn't have facial hair.
     "We agree that in the arrays, the lighting is slightly different for Mr. Worku's photograph and some of the 16 other photographs," Bacharach conceded, "but all are color photographs and depict Ethiopian men of similar ages. With these similarities among the men depicted, the court had the discretion to conclude that the differences in lighting would not have suggested which photograph to pick."
     Worku's "substantively unreasonable" claim implied that the 22-year sentence could not "be reconciled with the sentencing guidelines," Bacharach said.
     But district court had taken into account that Worku "was capable of torture," that he had "concealed his identity to avoid prosecution," and that his crimes were serious because they "corrupted the established processes of immigration and limited the prospects of truly deserving immigrants."
     Due to all of this, the district court was correct to impose the maximum sentence for each violation. Bacharach cited U.S. District Judge John Kane, whose sentence Worku appealed: "'Congress has provided maximum sentences for the most egregious violations of these statutes. If this case is not egregious, I cannot imagine what case would be.'"

Source : http://www.courthousenews.com/2015/09/02/22-years-for-torturer-ok-with-10th-circuit.htm