Thursday, October 22, 2015

የሞያሌ ወጣቶች ለውትድርና ምዝገባ የቀረበላቸውን ጥያቄ ውድቅ አደረጉት


ጥቅምት ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኢትዮጵያ ሞያሌ፣ የመንግስት ባለስልጣናት ወጣቶችን ለውትድርና ለመመዝገብ በድምጽ ማጉያ የታገዘ ቅስቀሳ ቢያካሂዱም፣ አንድም ለምዝገባው ፈቃደኛ ሆኖ የሄደ ወጣት አለመኖሩን ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ።
ወጣቶቹ የተደረገላቸውን የስብሰባ ጥሪ ባለመቀበላቸውም፣ መንግስት በሞያሌና አካባቢዋ አዳዲስ ምልምል ወታደሮችን ለመመዝገብ ያቀደው እቅድ ሳይሳካ ቀርቷል። አምና 10ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ወጣቶችን ለወትድርና ለመመዝገብ ማቀዱን የገለጸው መንግስት፣ ሂደቱ ውጤታማ ባለመሆኑ የትምህርት ደረጃ መስፈርቱን ወደ 8ኛ ክፍል ዝቅ አድርጎት ነበር። ይህም ሆኖ ተመዝጋቢ በመጥፋቱ የትምህርት ደረጃ መስፈርቱ ወደ 5ኛ ክፍል ዝቅ እንዲል ተደርጓል።
በደቡብ ክልል ሰሞኑን ሲካሄድ የቆየው የውትድርና ምዝገባ ባለመሳካቱ የአካባቢውን ሹማንምን አስድንግጧል። የዞን፣ የወረዳና የቀበሌ ባለስልጣናት እንደሚለምሉ የተሰጣቸውን የሰራዊት ቁጥር ለሟሟላት ባለመቻላቸው፣ ለስልጠናና ትምህርት በሚል ወጣቱን ለመመዝገብ ቢያቅዱም ይህም እቅድ ሳይሳካ ቀርቷል። መንግስት በየጊዜው በገፍ እየጠፉ የሚገኙትን የመከላከያ ሰራዊት አባላት በአዳዲስ ምልምል ወታደሮች ለመተካት በማሰብ ቅስቀሳውን መጀመሩን ምንጮች ይገልጻሉ።
በሁሉም አቅጣጫዎች የሚጠፉ ወታደሮች ቁጥር ከመቼውም ጊዜ በላይ መጨመሩን የሚደርሱን መረጃዎች ያሳያሉ።
Source:: Ethsat

No comments:

Post a Comment