Friday, September 25, 2015

የዲላ ዩኒቨርስቲ ሰራተኞች ኣመፅ ኣስነሱ


ከአምዶም ገብረሥላሴ

የዲላ ዩኒቨርስቲ ሰራተኞች በፕሬዝዳንታቸው “ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ ኮሬ” ላይ ዓመፅ በማስነሳት ወደ ትምህርት ምኒስቴር ጥያቄያቸው ልከዋል።
ፕሬዝዳንቱ “ዶክተር ኢንጅነር ስለሺ ኮሬ” ላይ 16 ክሶች ቀርቦላቸዋል።

ከክሰቹ መሃል
፩) ከ229 በላይ ሰራተኞች ከህግና ድንብ ውጪ በራሳቸው ስልጣን እንዲቀጠሩ ኣድርገዋል፣
፪)ሰራተኞች ዩኒቨርስቲው ለቀው እንዲሰደዱ እያደረጉ ነው።
፫) ለኢስትራክተሮችና ሰራተኞች የሚደበድብ ሃይል ኣደራጅተው ኣስደብድበዋል
፬ )በ ስልጣን ያለ ኣግባብ መጠቀም
፭) በኪራይ ሰብሳቢነት
፮) በሃብት ኣባካኝነት
፯) በጠባብነት
፰) “እኔ በሂወት እያለው የኣማርኛና ታሪክ ትምህርት ክፍል በዩኒቨርስቲው ኣላስከፍትም” የማለት ወዘት ያካተቱ 16 ጥያቄዎች ለትምህርት ምኒስቴር ምኒስትር ለሆኑት ኣቶ ሺፈረኣው ሽጉጤ ኣቅርበዋል።
ይህ የሰራተኞች ዓመፅ በታማኝ የዩኒቨርስቲ ሹሞኞች ላይ ኣዲስ ጅምር ነው።
በኣክሱም ዩኒቨርስቲም ፕሬዝዳንቱና ምክትሉ በተመሳሳይ ምክንያት ከቦታቸው እንዲነሱ ተደርገዋል።
መቐለ ዩኒቨርስቲም የሆነ የለውጥ ድባብ እያንዣበበ ይመስላል።
እየተጀመሩ ያሉት የለውጥ ጅምር ዩኒቨርስቲዎቻችን የምር ዩኒቨርስቲ ለመሆን የጀመሩት እንቅስቃሴ ይሆን…?
ነፃነታችን በእጃችን ነው።

Source:: Zehabesha

No comments:

Post a Comment