Wednesday, July 15, 2015

የግል አየር መንገዶች ከበራራ በፊት ለመከላከያ ሚኒስቴር ሪፖርት እንዲያደርጉ መጠየቃቸው ስራቸውን እንዳስተጓጎለ ገለጹ


ሐምሌ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኢትዮጵያ ውስጥ በመለስተኛ የግል የአውሮፕላን የበረራ አገልግሎት ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ባቀረቡት አቤቱታ፣ የስራ ዘርፉ ከቢሮክራሲ ጋር በተያያዘ ለኪሳራ እየዳረጋቸው መሆኑን ሳያንስ፣ ከበረራው 24 ሰአታት በፊት ለመከላከያ ሚኒስቴር ሪፖርት እንዲያደርጉ መታዘዛቸው ስራቸውን አስቸጋሪ አድርጎታል።
አንዳንድ ባለሀብቶች በተለይ ወደ ሰሜን የአገሪቱ ክፍል የሚደረገው በረራ ፈታኝ እንደሆነባቸው ገልጸዋል። አስቸኳይና ድንገተኛ በረራ የሚጠይቁ ድርጅቶች ወይም ግለሰቦች ሲመጡ፣ አፋጣኝ አገልግሎት መስጠት አልቻልንም ያሉ ሲሆን፣ የመንግስት ባለስልጣናት በበኩላቸው ” ሪፖርት የሚያደርጉት ላራሳቸው ደህንንነት ሲባል ነው የሚል መልስ ሰጠዋል። “በሰሜን አካባቢ የሚደረገው በረራ የደህንነት ስጋት ስላለበት፣ ማንኛውም አብራሪ በረራ ከማካሄዱ ከ24 ሰአታት በፊት ለመከላከያ ሪፖርት እንዲያደርግ መታዘዙ ተገቢ ነው ” የሚል መከራከሪያ በባለስልጣናቱ በኩል ቀርቧል።

No comments:

Post a Comment