Wednesday, July 15, 2015

አስራ ሁለት ስደተኛ ኢትዮጵያውያን ኬንያ ውስጥ ተይዘው ታሰሩ።


ሐምሌ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዴይሊ ኔሽን እንደዘገበው ኢትዮጰያውያኑ በምራባዊ የሀገሪቱ ግዛት በኢምቡ ክፍለ -ከተማ በኪቲሙ ገበያ አቅራቢያ በሚገኝ እርሻ ውስጥ ሊደበቁ ሲሞክሩ ነው የተያዙት።
ሁሉም ወንዶችና ከ30 ዓመት በታች የሆኑት ኢትዮጰያውያን ባካባቢው ነዋሪዎች ጥቆማ በበቆሎ ማሳ ውስጥ እንዳሉ መያዛቸውን የገለጹት የኢምቡ ኮሚሽነር፤ ሁሉም የኪስዋሀሊ ቋንቋን እንደማያውቁ አመልክተዋል።
በ አካባቢው ህገወጥ ስደተኞች ሲያዙ የ አሁኑ ለሁለትኛ ጊዜ ነው ብለዋል-ኮሚሽነሩ። ህገውጥ ስደተኞች የሚጓጓዙት በስቴሽን ዋገን እንደሆነ የአካባቢው ባለስልጣናትን በመጥቀስ ኮሚሽነር ጋቴቻ ተናግረዋል።
ኮሚሽነሩ አክለውም “ህገ ወጥ ስደተኞችን የሚያጓጉዙ ባለመኪናዎች ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ አስጠንቅቄያለሁ ብለዋል።

No comments:

Post a Comment