Friday, October 30, 2015

በደቡብ አፍሪካ ስደተኞች ላይ ያነጣጠረው ጥቃት ተፈጸመ


ጥቅምት ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ አፍሪካ ውስጥ በሚኖሩ ስደተኞች ላይ ኢላማውን ያደረገው ባለፈው ዓመት ተፈፅሞ የነበረው ዘግናኝ ግድያና ዘረፋ በግርሃምስቶን ከተማ ውስጥ ማገርሸቱ ተገልጿል።
የራሳቸውን አነስተኛ ሱቆች ከፍተው የሚተዳደሩና በተቀጣሪነት የሚሰሩ ስደተኛ ኢትዮጵያዊያን፣ሶማሊያዊያን፣ ባንግላዴሻዊያን፣የፓኪስታናዊያን ከ500 በላይ የሚሆኑ ቤተሰቦች ከዕለተ ሰኞ ጀምሮ ከስራ ቦታቸው ላይ ንብረታቸው እየተዘረፉ አካላዊ ጥቃቶች እንደተፈጸሙባቸውና በአሳሳቢ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል።
የስራአጦች ንቅናቄ በመሩት የዘረፋ መርሃግብር ላይ የከተማዋ የታክሲ ማኅበር አባላትም ተባባሪ በመሆን”የታክሲ አሽከርካሪዎች ለቃችሁ ካልወጣችሁ መኪኖቻችሁን እናቃጥላለን’ የሚል መፈክሮችን በመለጠፍ ከዘራፊዎቹ ጎን መቆማቸውን አሳይተዋል።
የጥቃቱ ሰለባ የሆኑት ሴቶችና ሕጻናትን ጨምሮ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ ያሉ ሲሆን የከተማዋ ከንቲባ በጠሩት ስብሰባ ላይ የፖሊስ አባላት አለመገኘታቸው ጉዳዩን ይበልጥ ውስብስብ እንዳደረገው ኦፒንየን ራዲዮ አክሎ ዘግቧል።
Source:: Ethsat

No comments:

Post a Comment