Friday, March 20, 2015

እሥረኞቹ የፖለቲካ ፓርቲዎች የቀድሞ መሪዎች የእምነት ክሕደት ቃል ሰጡ



በነዘላለም ወርቅአገኘሁ የክሥ ዶሴ በሽብርተኝነት የተከሰሱት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች የእምነት ክህደት ቃላቸውን እንዲሰጡ በዳኞች ሲታዘዙ “አሸባሪዎች እኛ ሳንሆን አሸባሪው ሕወሃት-ኢህአዴግ ነው” አሉ።
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አሥራ ዘጠነኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ በዋለው ችሎት ለሁሉም ተከሣሾች “ድርጊቱን አልፈፀምንም” በሚል ቃላቸውን እንደመዘገበ ገልጿል።
ፍርድ ቤቱ የአቃቤ ሕግ ምሥክሮች የሚቀርቡበትንም ቀን ቀጠሮ ሰጥቷል።
ለተጨማሪ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

No comments:

Post a Comment