Friday, March 20, 2015

በመስሊሙ ማህበረሰብ ላይ ህወሃት የዘረጋውን የጥላቻና የበቀል ዘመቻ ለመከላከል የወጣ የአቋም መግለጫ

MUslimH
ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች የተጣሰውን ህገመንግስታዊ መብት በህግ ለማስከበር የጀመሩት ሰላማዊ ትግል ድፍን ሶስት ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ ይህ ትግል በመላው አለም ሰላማዊ ትግልን መታገል ለሚሹ አርአያ ከመሆኑም ባሻገር በተለያዩ አለም አቀፍ ተቋማት እውቅናን ያገኘም ነው፡፡ በነዚህ መራራ ሶስት የትግል አመታት ህዝቡ በፊርማው የመረጣቸው የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች የእስር ብቻ ሳይሆን የድብደባ፣ የግርፋት፣ የማዋረድ፣ የሰብዓዊ መብትም መገፈፍ ሰለባ ሆነዋል፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ሲታሰሩ፣ ሲገረፉ፣ ቁጥራቸው በውል የማይታወቅ ደግሞ ለመሰደድ በቅተዋል፡፡ሰላማዊ ዜጎች በግፍ ጥይት እየተደበደቡ ለሞት መዳረጋቸው ሊካድ የማይችል የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡

No comments:

Post a Comment