Wednesday, November 18, 2015

አገር አቀፍ የሳይንስና ቴክኖሎጂ የፈጠራ ሽልማት አሸናፊ “ሽብርተኛውን“ ተዋወቁት::በማያውቀው ክስ ቅሊንጦ ማረሚያ ቤት ዞን2 ይገኛል፡፡


አብርሃም ሰለሞን ይባላል ፡፡ በነ ዘላለም ወርቃለማው የክስ መዝገብ ከአራቱ የፓለቲካ አመራሮች በተከሰሱበት መዝገብ ስድተኛ ተከሳሽ የሆነው አብርሃም ሰለሞን መምህር ነበር ፡፡ አብርሃም ከመታሰሩ በፊት ቤተል ትምህርት ቤት መምህር ነበር ፡፡ በሞያውም የፈጠራ ስራዎች ላይ ማተኮር ይወድ ስለነበር አገር አቀፍ የሳይንስና ቴክኖሎጂ የፈጠራ ሽልማት አሸናፊ በመሆን ከተመረጡ መምህራንም መካከል አንዱ ነው ፡፡

ነሃሴ ላይ ከታሰረ በኋላ ጥቅምት ላይ በተደረገው አገር አቀፍ የሳይንስ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ሽልማት ተሸላሚ በመሆኑ በጥቅምት ወር በተደረገው የሽልማት ስነስርአት እናቱ ወክለውት ሽልማቱን ተቀብለዋል ፡፡ ይህ በሽብር የተከሰሰ ወጣት አስተማሪ አይሲቲን በቀላሉ እና በሚገባ መልኩ ማስተማር የሚረዳ የፈጠራ ውጤት ባለቤት በመሆኑ ነው ሽልማት ያገኘው ፡፡ የሽልማቱ ቲሸርት እና ሜዳልያን ይዘው ሊጠይቁት የሄዱት እናቱ ሜዳልያውን ማስገባት ባይችሉም ቲሸርቱን አስገብተውለት ተመልሰዋል ፡፡ በማስተማር እና በፈጠራ ስራ የተሰማራው ይህ መምህር አንድም እውነተኛ ሽብተኛ ተከሶበት በማያውቀው ክስ ቅሊንጦ ማረሚያ ቤት ዞን2 ይገኛል፡፡ በእርሱ የመምህርነት ደሞዝ ይተዳደሩ የነበሩ ቤተሰቦቹም እሱን ቅሊንጦ ድረስ እየሄዱ በመጠየቅ እየተንከራቱ ይገኛሉ ፡፡
ቢያንስ ኢንተርኔት ላይ ሼር በማድረግ የማናውቃቸው ብዙዎች ለሚከፍሉት ዋጋ እውቅናን እንስጥ
አብርሃም ሰለሞን

















አብርሃም ሰለሞን


Source: http://www.mereja.com/amharic/473887

No comments:

Post a Comment