Tuesday, August 25, 2015

ኢትዮጵያዊያን አሁንም በመተማ በኩል መፍለሳቸውን አላቋረጡም


ነኅሴ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያዋ የድንበር ከተማዋ መተማ አሁንም ኢትዮጵያዊያን መሰደዳቸውን አላቋረጡም ሲል ዘጋርዲያን ዘገብዋል።
መንግስት ጥበቃውን አጠናክሮ በአካባቢው ብዙ ሰራዊት ቢያሰማራም በቀን ከ100 እስከ150 የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞ ድንበር አቋርጠው ይሰደዳሉ።
መተማ ከተማ ወደ መቶ ሽህ የሚገመት ነዋሪዎች ያላት ስትሆን የኢትዮጵያ፣ ኤርትራና ሶማሌ ስደተኞች መተላለፊያ ናት።ከተማዋ መንግስት በወሰደው የጥበቃ ማጠናከር ሳቢያ ገቢዋ መቀዝቀዙንም ፣ 80% የሚሆነው የከተማዋ ገቢ የሚገኘውም ከሕገወጥ ስደተኞች መሆኑንም ዘጋርዲያን አትቷል።
ከዚህ ቀደም በቀን ከ250 በላይ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ይሰደዱ ነበር። መንግስት ጥበቃውን ያጠናከርኩት ኢትዮጵያውያን ሊቢያ ውስጥ በአይሲስ ከተገደሉ በኋላ ነው ቢልም፣ የአካባቢው ሰዎች ግን ጥበቃው የተጠናከረው ወጣቱ የመንግስት ተቃዋሚዎችን ለመቀላለቀል በገፍ ወደ ኤርትራ እየፈለሰ መሆኑን ተከትሎ ነው ይላሉ።
ምንም እንኳ የድንበር ጥበቃው ተጠናክሮ ቢቀጥልም፣ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እያደረጉ በትጥቅ ትግል ስርአቱን ለማስወገድ የሚታገሉ ሃይሎችን እየተቀላቀሉ ነው።

No comments:

Post a Comment