Tuesday, August 18, 2015

በአፋር ክልል በባለስልጣናቱ የስልጣን ሽኩቻ 4 ወጣቶች ታሰሩ


ኣቶ ሱዩም ኣወል
የኣፋር ክልል ፕረዝደንት የነበሩት ኣቶ ኢስማዒል ዓሊ ሲሮ ስልጣን መልቀቃቸዉን ተከትሎ በክልል ካቢኔ ዉስጥ በተፈጠረው የስልጣን ይገባኛል ውዝግብ፣ የአንዱ ቡድን ድጋፊዎች ናቸው የተባሉ አራት ወጣቶች ትናንት ታስረዋል።
1ኛ. አቶ ማሃመድ ኣመድ
2ኛ. አቶ ብልዓ ማሄ
3ኛ. አቶ ማሃመድ ኡመር
4ኛ. ፖሊስ ዳዋ ማሃመድ
የተባሉ ወጣቶች ትናንት ድንገት ባልታወቀ ሁኔታ ታስረው እስካሁን ፊርድ ቤት የት እንዳሉ አይታወቅም።
በአፋር ክልል ምን ጊዜም ቢሆን የበላይንት የሚሰማው አቶ ስዩም ኣወል የኣፋር ወጣቶችን ስያስሩ ዛሬ የመጀምሪያቸው ባይሆንም ዛሬ ግን ብሶበታል ይላሉ የኣፋር ወጣቶች።
ካሁን በፊት ኣቶ ኣዳን ሃባና የተባለ ግልሰብ ያለ ምንም ክስ በኣቶ ሱዩም ሴራ ታስሮ ሶስት ኣመት ያለ ምንም ፊርድና ፊትህ ታስሮ ይገኛል።
ኣቶ ሱዩም ኣወል
ለመሆኑ ኣቶ ሱዩም ኣወል ማን ናቸው ?
ኣቶ ሱዩም ኣወል የኣፋር ክልል የጸጥታ ዘርፍ ቢሮ ኃላፊ ሲሆኑ የክልሉ ፖሊሶች እንዳሻቸው ማዘዝ የሚችሉ፣ በክልሉ ሙሉ በሙሉ በ1ርብ ቤተሰቦቻቸው የሚመራ ልዩ ፖሊስ ያላቸው፣ ኣሁን ከስልጣን የተንሱት ኣቶ ኢስማዒልን እንደ ልጃቸው ያስፈራሩ የነበሩ፣ከኣፋር ሽማግለዎች ጋር ፍጹም የዋህ መስለው የሚቀርቡ፣ ግን የመጨረሻ ያልታወቁ እባብ የሆኑ የእነ ገብረጽዮን ገብረሚካኤል ቀኝ እጅ የሆኑ፣ ትንሽ ራስ ምታት ሲሰማቸው በቀላሉ ታይላንድ ባንኮክ ታክመው የሚመለሱ፣በየኣመቱ ለይስሙላ ሳኡዲ ኣራቢያ ለሀጅ ደርሰው የሚመለሱ፣ በክልል ፖሊስ እና ልዩ ፖሊስ ከመቶ ኣለቃ እስክ ኩማንደር የራሳቸው ቅርብ በተሰቦች የሾሙ፣ ኣዲስ ኣበባን ጨምሮ በኢትዮጲያ ብትላልቅ ከትሞች ኣሉ የሚባሉ ህንጻዎች የገነቡ፣ የወያኔ ቁጥር ኣንድ ካድረ ናቸው።
ኣሁንም ቢሆን በክልሉ እንደ ኢስማዒል ሲሮ እንደፈልግኩት ማዘዝ የሚችለው መሪ ካልሾምክ በማለት የተቃወመዉን ሁሉ ማሰር ማሳቃየት ቀጥለዋል።
Source:: Zehabesha

No comments:

Post a Comment