Saturday, February 28, 2015

የጉራጌ ካድሬዎች አንገታቸውን ያስደፋ ክስተት

‹‹ያለ ኢኮኖሚ የበላይነት የፖለቲካ የበላይነት አይመጣም››
የሚለው የህውሃት ኢህአዲግ ፖለቲካ ኢኮኖሚውን ከመቆጣጠር ባለፈ ደጋፊዎቹን በኢኮኖሚ በማብቃትና በተጠቃሚነታቸውም ፖለቲካውን በመጠበቅ የበረኛነት ሚና እንዲጫወቱ በ97 ምርጫ ማግስት ከተወሰዱትርካሽ እርምጃዎች አንዱ በግምታዊ አቀማመጥ መሃከለኛ ገቢ ያላቸውን የመርካቶ ጉራጌዎች በማዳከም የህውሃትን ተጠቃሚዎች ማጠናከር ነበር::
የወቅቱ የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዲኤታ ኤርሚያስ ለገሰ ይህንን ይላል

በምርጫ 97 ማግስት አቶ መለስና በረከትን ጨምሮ ከፍተኛ የኢህአዴግ ካድሬዎች ‹‹ጉራጌ አብዮት አካሄደብን›› በማለት ይናገሩ ነበር፡፡ በኢህአዴግ ማእከል በተዘጋጀው ሰነድ ላይ የጉራጌ ብሄረሰብ ከትምክህት ጎራ ጋር በተቀላቀሉ ልጆቹ ምክንያት የሀይል አሰላለፍ ቀውስ ውስጥ በመግባት ከጥገኛ ኃሎች ጋር ተሰልፎ ወደ ዝቅጠት ገብቶ እንደነበር ይገልጻል፡፡ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የብሄረሰቡ ተወላጆች(በጉራጌ ዞን ያለውን መዋቅራችንን ጨምሮ) የዜጎችን በነጻነት የማሰብና የመምረጥ መብት በመጋፋት እስከ ጎጣቸው በመሄድ ‹‹ኢህአዴግን የመረጠ ውሻ ይውለድ!›› የሚሉ ቃል ኪዳኖችን እስከ ማጥለቅና መማማል ዘልቀው ነበር በማለት ይከሳቸዋል፡፡ የጉራጌ ብሄረሰብ እንደ ሌሎች የሀገራች ጭቁን ብሄረሰቦች ህገ-መንግስታዊ መብቱ በተከበረበት፣ ራሱን በራሱ የማስተዳደር መብት በተጎናጸፈበት ሁኔታ ወደ ትምክህት ሀይል ሽግሽግ ማድረጉ ያልተጠበቀ እንደነበር ሰነዱ አመላከተ፡፡( ቅንፍ የራሴ በምርጫ ኢህአዴግን አለመምረጥ መብት ሳይሆን ትምክህተኝነት የሚባል ሃጥያት ነበር ዛሬም ነው)
በቀረበው ዶክመንት ላይ በመመስረት በየወረዳው የተካሄዱት መድረኮች አስደንጋጮች ነበሩ፡፡ የምርጫ 97 ውጤት የኢትዮጵያ ህዝቦች የትግ ውጤት መሆኑን በመካድ ‹‹ጉራጌ መራሽ አብዮት›› የሚል ስያሜ እስከ መስጠት ተደረሰ፡፡ ጣቶች በሙ ወደ ጉራጌ ብሄረሰብ በተለይም የብሄሩ ተወላጅ የኢህአዴግ ካድሬዎች ላይ ተቀሰሩ፡፡ ነጋዴው ጸረ-ኢህአዴግ እንዲሆን ከአመታት በፊት የተጠነሰሰ ሴራ እደሆነ በሰፊው ተነገረ፡፡ የጉራጌ ካድሬዎች አንገታቸውን ደፉ፡፡
:
:
ኢኮኖሚውን የሚቆጣጠር ኃይል በሂደት ፖለቲካ ኢኮኖሚው ላይ የበላይነት ማሳረፉ ስለማይቀር ጉራጌን ከንግዱ ዓለም ማስወጣት ለጥያቄ የሚቀርብ አይደለም፡፡ ሮማን (የህወሃት ባለሃብቶችን መፍጠር አላማ አስቀጣይ የሆነች) የጉራጌ ነጋዴዎችን እንዳያሰራሩ የምትቀጣበት ምክንያት ይህ ነበር፡፡
እነ ሮማ በፈጠሩት ልዩነት ጉራማሌዋ መርካቶ ይበልጥ ተዘበራረቀች፡፡ ተመሳሳይ እቃዎች በነባሮቹና አዲሶቹ ነጋዴዎች መካከል የዋጋ ልዩነት አሳየ፡፡ የግብርና የሊዝ እፎይታ ያገኙት አዲሶቹ ነጋዴዎች ዋጋቸውን አወረዱ ሸማቹሚስጥሩ ሳይገባው ቅናሽ ወዳገኘበት አዲሶቹ ነጋዴዎች ፊቱን አዞረ፡፡ ቀስ በቀስ ነጋዴው ከገበያ ወጣ፡፡
የማፊያ ባህሪ ያላቸው አዲሶቹ ነጋዴዎች ሰው ሰራሽ እጥረት በመስከሰትም ተወዳዳሪ አልነበራቸውም፡፡ በሰአታት ውስጥ አንድ ኪሎ ጨው ዋጋ ከአንድ ብር 50 ብር የተሸጠበት አጋጣሚ ልብ ይሏል፡፡
ነባሩ ነጋዴ ከገበያ መውጣቱ እልህ የተጋቡት የጉራጌ ካድሬዎቹ እነ ሺሰማ ክትትል ማድረግ ይጀምራሉ፡፡ ከብዙ ጥረት በኋላ ሸፍጥ የሚሰራበትን ቦታ ይደርሱበታል፡፡ ሮማንና ወዳጆቿ ፋይል የሚሰርዙና የሚደልዙት፣ ግብር የሚጨምሩትና የሚቀንሱት፣ ሱቅ የሚሰጡትና የሚቀሙት አምባሳደር ፊልም ቤት የሚገኘው ካፍቴሪያ የሕገወጥነቱ ማዕከል ነበር፡፡….
ከምርጫ 97 በኋላ የጉራጌ አብዮትን ለመቀልበስ በስብሰባ ማዕከል በተጠራ የመጀመሪያው ዙር ማጠቃለያ ኮንፍረንስ ላይ ተገኝቼ ነበር፡፡ በጉባኤው የተሳተፉት ከአንድ ሺህ በላይ የጉራጌ ነጋዴዎችና ባለሃብቶች ነበሩ፡፡ ይህን ለአንድ ሳምንት የዘለቀ ጉባዔ የመራው ዶ/ር ካሱ ኢላላና ሚኒስትር መኩሪ ነበሩ፡፡ ነጋዴዎች በሲቃ ስለ ሮማንና ሉሌ የሚነሱት ወንጀል ጨጓራ የሚልጥ ነበር፡፡ በተለይ የክፍለ ከተማው የገቢዎች ኤጀንሲ ሙያተኛ የሆነ የጉራጌ ተወላጅ ስራየን ለመልቀቅ ብዙ ተሟግቻለሁ በማለት የገለጸው ታሪክ ዶ/ር ካሱ አንገቱን አቀርቅሮ አንዲቀር አድርጎታል፡፡ ከመቀመጫው ተነስቶ የኮንፈረንሱን ተሳታፊ አንባ እየተናነቀው ይቅርታ ጠይቋል፡፡
እንዲህ ነበር ያደረጉት፣
ሎሌና ሮማን ከቢሮአቸው ሳይወጡ ከአስር እጥፍ በላይ ግብር እንዲጥሉ ሙያተኞችን አስገደዱ፡፡ ከስረው ለመዘጋት አፋፍ ላይ ያሉ ነጋዴዎችን ከግብር ሕጉ በተቃራኒ ታክስ አስከፈሉ፡፡ በድርጊቱ የተበሳጨ አንድ ነጋዴ ራሱን በገመድ አንጠለጠለ፡፡ ተመሳሳይ ሱቅና የንግድ ዓይነት ያላቸውን ጎረቤት ነጋዴዎች አንዱን በዜሮ ፣ሌላውን በአስር ሺዎች ታክስ እንዲከፍል አድርገዋል፡፡ ይህ በዘር ላይ የተመሰረተ እርምጃ ቀድሞ በነጋዴዎች ዘንድ የነበረን በደጋገፍ እንዲቀር በማድረግ እርስ በራስ በጥላቻ እንዲተያዩ አድርጓል፡፡ በዚህ ምክንያት መሳሪያ የተማዘዙ፣ በገጀራ ተፈነካክተው ወህኒ የወረዱ ነጋዴዎች ይገኙበታል፡፡
(ለግምገማ ቀርባ የነበረችው ሮማን እንዳትጠየቅ አርከበ ተከላክሎ አትርፏታል)
posted by Aseged Tamene

No comments:

Post a Comment