Sunday, July 26, 2015

ሐሳብን ከመግለጽ ነጻነት ጋር በተያያዘ በኢትዮጵያ እስር ቤቶች ከሚገኙ ጋዜጠኞችና ጦማርያን የተወሰኑት

 

* ሁሉም የታሰሩለት አላማ እስኪፈታ ድምጻችንን እናሰማለን
1. እስክንድር ነጋ (በህገ ወጥ መንገድ በሞያው እንዳይሰራ የታገደ በኋላም በግንቦት ሰባት አባልነትና የአረቡን አለም አይነት አብዩት በኢትዩጵያ እንዲፈጠር ታደራጃለህ ተብሎ 18 ዓመት የተፈረደበት ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት ተሟጋች)
2. ውብሸት ታዬ (የቀድሞዋ አውራምባ ታይምስ ምክትል ዋና አዘጋጅ ‹‹ህዝቡ የት ገባ››በማለት በመጠየቁ 14 ዓመት የፈረደበት)
3. ተመስገን ደሳለኝ (ስርዓቱ በህትመት ውጤቶቹ ላይ የሚወስድበትን አፈና በዘዴ በመቋቋም ትውልዱን ‹‹የፈራ ይመለስ ››በማለት በማጠየቁ ሶስት ዓመት ተፈርዶበት ለወህኒ የተዳረገ ደፋር ጋዜጠኛ)
4. የሱፍ ጌታቸው(በሙስሊም ኢትዮጵያዊያን ልብ ልዩ ስፍራ በሚሰጣት የሙስሊሞች ጉዳይ መጽሔት በዋና አዘጋጅነት በመስራቱ የተከሰሰ)
5.ሰለሞን ከበደ(የሙስሊሞች ጉዳይ መጽሔት ማኔጂንግ ኤዲተር ያልተነገረለት ምርጥ ጋዜጠኛ)
6.እስማኤል ዳውድ (በሚልዩኖች ድምጽ ጋዜጣ ያቀርባቸው በነበሩ ጽሁፎች ተስፋን ፈንጥቆ የነበረ ብዕረኛ)
6. ሃብታሙ ምናለ(ከአንድ እትም በላይ እድሜ እንዳይኖራት በተደረገችው ቀዳሚ ገጽና በሚልዩኖች ድምጽ ይሰራ የነበረ ስርዓቱ ኦባማ ላይ የሽብር ጥቃት ለማድረስ ከአልሻባብ ጋር ተማክረሃል በማለት አስሮታል)
7. በፍቃዱ ኃይሉ የዞን ዘጠኝ አባል ፣የዕንቁ መጽሔት ኤዲተር እንዲሁም የመጽሐፍ ደራሲ
8. አቤል ዋበላ የዞን ዘጠኝ አባል
9. አጥናፍ ብርሃኔ — የዞን ዘጠኝ አባል
10. ናትናኤል ፈለቀ –የዞን ዘጠኝ አባል
11.አብርሃ ደስታ — በማህበራዊ ድረ ገጾች በዋናነት ህወሓት በትግራይ ህዝብ ላይ የሚያደርሰውን በደል ያጋልጥ የነበረ

‪#‎Free‬ all Prisoners of Conscience

No comments:

Post a Comment